"ሰብአዊነትና ፍቅር ለትግራይ እና ለመተከል" በሚል ሀሳብ ስር ጥምረት በመፍጠር የድጋፍ ማሰባሰብ እንቅስቃሴዎችን በማድረግ ላይ የቆየው ቡድን ከ20 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ መሰብሰቡን አስታወቀ።
የጥምረቱ ሰብሳቢ አርቲስትና የሰብአዊ መብት ተሟጋቹታማኝ በየነ ትናንት በሰጠው መግለጫ ላይ እንዳስታወቀው፤ በትግራይ እና በመተከል ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች ተብሎ በተከፈቱ የባንክ አካውንቶች 20 ሚሊዮን 716 ሺህ 559 ብር ገቢ ተገኝቷል።
በተመሳሳይ በጎፈንድሚ በውጭ አገራት በተከፈተው የገንዘብ ማሰባሰቢያ መርሀ ግብር ደግሞ 210 ሺህ ዶላር መገኘቱን አስታውቋል።
በአይነት በተደረገ ድጋፍም ግምቱ አንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን ብር ዋጋ ያለው ርዳታ መገኘቱንም ታማኝ ገልጿል።
የተሰበሰበው ርዳታ ከዛሬ ጀምሮ ወደሁለቱም አካባቢዎች መጓጓዝ እንደሚጀምር አርቲስ ታማኝ በየነ አስታውቋል።

