የቀድሞዋ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ኬሪያ እጃቸውን መስጠታቸው የመንግሥት የትግራይ ግብረ ኃይል "ከሕወሓት ዘጠኝ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አመራር አባላት አንዷ የሆኑት ኬሪያ ኢብራሂም ለፌዴራል ኃይሎች እጃቸውን ሰጥተዋል" ሲል ገልጧል።
ወ/ሮ ኬሪያ በወርኃ ጁን ለትግራይ ቴሌቪዥን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ከኃላፊነታቸው በገዛ ፈቃዳቸው መነሳታቸውን አስታውቀው ነበር።
የሳቸውን መግለጫ ተከትሎም ምክር ቤቱ "አፈ ጉባኤዋ ራሳቸው በጠሩት መደበኛ ስብሰባ ዋዜማ የሥራ መልቀቂያ ሳያስገቡ ከኃላፊነታቸው መልቀቃቸውን መግለጣቸው የምክር ቤቱን ደንብ ያልተከተለ ነው። የአፈ ጉባኤዋ ስንብትም የምክር ቤቱን ሂደት አያስተጓጉልም" ማለቱ ይታወሳል።
Share

