ተጠባቂው የሴቶች ሩጫ ውድድር

*** በቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ውድድር ኢትዮጵያ ከብርና ነሃስ በላይ የወርቅ ሜዳልያ የምትጠብቀው በሴቶች 10 ሺህ ውድድር ነው።

Tokyo 2020 Olympic Games

Roza Dereje of Team Ethiopia (C) compete in the Women's Marathon on day fifteen of the Tokyo 2020 Olympic Games at Sapporo Odori Park on August 07, 2021. Source: Getty

ኢትዮጵያ በዘንድሮው የቶኪዮ ኦሎምፒክ እስካሁን ከተካሄዱ ውድድሮች ወርቅ ያገኘችው በወንዶች 10 ሺህ ሩጫ ብቻ ነው።

ትናንት በተካሔደው የሴቶች ማራቶን ውድድር ሮዛ ደረጀ 2:28:38 በማጠናቀቅ አራተኛ በመሆን ጨርሳለች። ብርሃኔ ዲባባና ዘይነባ ይመር ውድድሩን ሳያጠናቅቁ አቋርጠው ወጥተዋል።

በዚህ የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ውድድር ኢትዮጵያ ከብርና ነሃስ በላይ የወርቅ ሜዳልያ የምትጠብቀው በ10 ሺህ ውድድር ነው።

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ይፋ እንዳደረገው ዛሬ በአውስትራሊያ ሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ 8:45pm ጀምሮ በሚካሄደው በዚህ ተጠባቂ ውድድር ኢትዮጵያ በ10 ሺ ሜትር ፍፃሜ ለተሰንበት ግደይ፣ ፅጌ ገ/ሰላማና ፀሀይ ገመቹ አማካኝነት ትወከላለች።

በርካታ ኢትዮጵያውያን ውድድሩን በጉጉት እየተጠባበቁ እንደሚገኙ በሶሻል ሚዲያ እየገለፁ ይገኛሉ።

[ ደመቀ ከበደ ፡ አዲስ አበባ ]


1 min read

Published

Updated

By Demeke Kebede


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now