በቶኪዮ 2020 ኦሎምፒክ የአትሌቲክስ ውድድር ሠንጠረዥን ተከትሎ በተጀመረው የ3000 ሜትር ወንዶች የማጣሪያ ዙር የተሳተፉ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በቀዳሚና ተከታይነት ለቀጣይ ዙር አልፈዋል።
በውድድሩም፤
- ለሜቻ ግርማ 8:09:83 በመጨረስ ከምድቡ አንደኛ ሆኖ ሲያልፍ

- ጌትነት ዋለ በኬንያዊው ኪቢዎት ተቀድሞ 8:12:55 በማጠናቀቅ በሁለተኛ ደረጃነት ለቀጣይ ዙር ውድድር ተሻግረዋል።

- በሴቶች የ800 ሜትር ማጣሪያ ውድድር ሀብታም ዓለሙ 2:01:20 ጨርሳ በሁለተኛነት ከምድቧ አልፋለች።

ዛሬ ማምሻውን በአውስትራሊያ ሰዓት አቆጣጠር 9፡30pm ጀምሮ የወንዶች 10000 ሜትር የፍጻሜ ውድድርና የሴቶች 5000 ሜትር ማጣሪያ ውድድሮች ይከናወናሉ።
በወንዶች 10000 ሜትር ፍጻሜ ተወዳዳሪዎቹ ዮሚፍ ቀጀልቻ፣ ሰለሞን ባረጋና በሪሁ አረጋዊ ለኢትዮጵያ የወርቅ ሜዳል የማስገኘት ዕድል ሰፊ ሆኖ ይጠበቃል።
በሴቶች 5000 ሜትር ማጣሪያ ተፎካካሪዎቹ ጉዳፍ ፀጋይ፣ ሰንበሬ ተፈሪና እጅጋየሁ ታየ በማጣሪያ ዙር ውድድራቸው ወደ ቀጣዩ ዙር የሚያሸጋግራቸውን ውጤቶች በማግኘት ያልፋሉ ተብሎ ከፍተኛ ግምት ተጥሎባቸዋል።
በቶኪዮ ኦሎምፒክ መክፈቻ ሥነ ሥር ዓት ላይ የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ አውለብሎ የነበረው አብዱልማሊክ ሙክታር በ50 ሜትር ነፃ የቀዘፋ ዋና ማጣሪያ ይወዳደራል።

