ኢትዮጵያውያን ሴት አትሌቶች በ800 እና 5000 ሜትሮች የማጣሪያ ውድድሮችን በአሸናፊነት እያለፉ ነው።
ትናንት ጁላይ 30 በቶኪዮ ኦሎምፒክ ስታዲየም በተካሔደው የ5000 ሜትር የመጀመሪያ ዙር ማጣሪያ ውድድሮች፤
- ሰንበሬ ተፈሪ 14:48:31
- እጅጋየሁ ታየ 14:48:52
- ጉዳፍ ፀጋይ 14:55:74 በሆነ ውጤት ሰኞ ኦገስት 2 ምሽት ለሚካሔደው የፍፃሜ ውድድር አልፈዋል።
የ5000 ሜትር የዓለም ክብረ ወሰን በኢትዮጵያዊቷ ለተሰንበት ግደይ ተይዞ ይገኛል።
ለተሰንበት እ.አ.አ በ2020 በቫሌንስያ ስፔይን የተካሔደውን የ5000 ሜትር ውድድር አዲስ የዓለም ክብረ ወሰን በማስመዝገብ ያጠናቀቀችው 14:06:62 በሆነ ውጤት ነው።

በሴቶችና በወንዶች የ800 ሜትር ውድድሮች በትናንትናው ዕለት ተወዳዳሪ ከነበሩት ውስጥ፤
- ሃብታም ዓለሙ 2:01:20 በመጨረስ ዛሬ ማምሻውን ለሚካሔደው የግማሽ ፍፃሜ ውድድር አልፋለች
- ነፃነት ደስታ 2:01:98 በማጠናቀቅ ለቀጣዩ ውድድር ሳታልፍ ቀርታለች
- በወንዶች ውድድር መለስ ንብረት 1:47:80 በመጨረስ በለስ ሳይቀናው ከውድድሩ ተሰናባች ሆኗል።

