ሰለሞን ባረጋ የመጀመሪያውን የኢትዮጵያ የቶኪዮ ኦሎምፒክ ወርቅ ሜዳል ተቀበለ

*** ሃብታም ዓለሙ ለ800 ሜትር፤ ዘርፌ ወንድማገኝና መቅደስ አበበ ለ3000 ሜትር የሜዳል ውድድር አለፉ

Tokyo 2020 Olympic Games

Gold medallist Ethiopia's Selemon Barega celebrates on the podium for the men's 10000m event during the Tokyo 2020 Olympic Games on July 31, 2021. Source: Getty

በ10000 ሜትር የቶኪዮ ኦሎምፒክ የሩጫ ውድድርን በአንደኛ ደረጃ አሸናፊነት የተወጣው አትሌት ሰለሞን ባረጋ የወርቅ ሜዳል ተቀበለ።

ለኢትዮጵያ በቶኪዮ ኦሎምፒክ የመጀመሪያ የሆነውን የወርቅ ሜዳል ያስገኘው ሰለሞን የ10 ሺህ ሜትር ውድድሩን በአሸናፊነት የደመደመው 27:43:22 በመጨረስ ነው።

Tokyo 2020 Olympic Games
Ethiopia's Selemon Barega celebrates after winning the men's 10000m final during the Tokyo 2020 Olympic Games at the Olympic Stadium in Tokyo on July 30, 2021. Source: Getty

ትናንት ማምሻውን በተካሔደው የሴቶች 800 ሜትር የግማሽ ፍፃሜ ውድድር ዘርፌ ወንድማገኝ 92001 በሆነ ውጤት፤ እንዲሁም ሃብታም ዓለሙ 1:58:40 በማጠናቀቅ የዩናይትድ ስቴት ሷን ሙ አቲንግ ተከትላ ከምድቧ በሁለተኛ ደረጃ አሸንፋ ለፍጻሜ ውድድር አልፋለች። 

Tokyo 2020 Olympic Games
USA's Athing Mu (R) and Ethiopia's Habitam Alemu react after crossing the finsh line of the women's 800m semi-final during the Tokyo 2020 Olympic Games. Source: Getty

የ800 ሜትር የፍፃሜ ውድድር ኦገስት 3 ማክሰኞ ምሽት 10:25pm ይካሔዳል።

በወንዶች 800 ሜትር ውድድር ለማጣሪያ ያለፈ አትሌት ባለመኖሩ ኢትዮጵያ በወንዶች 800 ሜትር ውድድር አትሳተፍም።

በሴቶች 3000 የመሰናክል ሩጫ ውድድር መቅደስ አበበ 9:23:95 በማጠናቀቅ ኦገስት 4 ከምሽቱ 21:00 ለሚካሔደው የፍፃሜ ውድድር አልፋለች።

Tokyo 2020 Olympic Games
(From L) Germany's Elena Burkard, Kenya's Hyvin Kiyeng, Ethiopia's Mekides Abebe and Slovenia's Marusa Mismas-Zrimsek compete in the women's 3000m steeplechase Source: Getty

ኢትዮጵያ ለቶኪዮ ኦሎምፒክ በዘጠኝ የውድድር መስኮች 34 ተወዳዳሪዎችን አሰልፋለች።  


1 min read

Published

Updated

By Kassahun Seboqa Negewo


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now