የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) በፌዴራል መንግሥቱና በሕወሓት መካከል በተፈጠረው ሶስት ሳምንታትን ያስቆጠረ ግጭት ሳቢያ በአገር ውስጥ ለተፈናቀሉና የሱዳንን ድንበር ተሻግረው ለስደት ለተዳረጉ ኢትዮጵያውያን መርጃ እንዲውል $35.6 ሚሊየን መቸሩን በዲሴምበር 17 መግለጫው አስታወቀ።
የ$13 ሚሊየን ችሮታው ወጪ የተደረገው ከተመድ ማዕከላዊ የአስቸኳይ ግብረ ምላሽ ድጎማ ሲሆን የሚውለውም ኢትዮጵያ ውስጥ ለተፈናቀሉ ዜጎች ሲሆን፤ ተጨማሪ $5 ሚሊየን ሱዳን በቅርቡ በስደተኛነት ለገቡቱ መርጃ ይውላል። በታካይነትም $12 ሚሊየን ከኢትዮጵያ የተመድ ሰብዓዊ እርዳታ ድጎማና $5.6 ከሱዳን የተመድ ሰብዓዊ እርዳታ ድጎማ ወጪ ሆኗል።
በእርዳታ ክፍፍሉም ወቅት ለሴቶች፣ ሕጻናት፣ አረጋውያንና የግብረ አካል ጉዳተኞች ቅድሚያ እንደሚሰጥ ተመድ ገልጧል።
የመንግስታቱ ድርጅት አያይዞም "እንዲህ ያሉ ግጭቶች አንዴ ከቁጥጥር ውጪ ከሆኑ ለማስቆም በእጅጉ አዋኪ ነው። የተቀጠፉ ሕይወቶች አይመለሱም፤ ዘላቂ ዕርሮዎችንም ይፈጥራሉ። በአሁኑ ወቅት ሕጻናት ከእርዳታ ተገልለዋል። ያልተገደበ ተደራሽነት እንዲኖረን እንሻለን" ብሏል።

