ቪክቶሪያና ኩዊንስላንድ የሞባይል ስልኮችን የሚቆጣጠሩ ካሜራዎችን ጠመዱ

***በካሜራዎቹ የተያዙ የቪክቶሪያ ሾፌሮች $496 የኩዊንስላንድ አሽከርካሪዎች $1000 ይቀጣሉ

mobile

A young driver looks down at her cell phone to read a text message as she drives at the same time. Source: AP

ቪክቶሪያ ከመሪ ኋላ ሆነው የሞባይል ስልክ የሚጠቀሙ አሽከርካሪዎችን ተቆጣጥረው የሚቀርጹ ካሜራዎቿን ከዛሬ ጁላይ 29 ጀምሮ የመጀመሪያ የሙከራ ተግባራቸው ላይ አሰማርታለች።

የቴክኖሎጂ ሙከራ ጊዜው የሚቆየው ለሶስት ወራት ሲሆን ከዚያ በኋላ በቋሚነት የቁጥጥር ሥራ ላይ ይውላል።

ኩዊንስላንድም በበኩሏ ከዚህ ሳምንት ጀምራ እስከዚህ ዓመት መጨረሻ የሚቆይ የሞባይል ስልክ የካሜራ ቁጥጥር ሙከራዋን ትጀምራለች።

የኩዊንስላንድ ሙከራ ሞባይል ስልኮችን ብቻ የሚመለከት ሳይሆን የመኪናቸውን ቀበቶ ያልታጠቁትንም ያካትታል። 

ሁለቱ ክፍላተ አገራት በሙከራ ጊዜያቶች ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ አውቶሞቢሎችን እያሽከረክሩ ሞባይል ስልኮቻቸውን ሲጠቀሙ በካሜራ ለተደረሰባቸው ሰዎች የመቀጮ ሳይሆን የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ እንዲደርሳቸው ያደርጋሉ።

Mobile phone detection cameras
Source: Courtesy of PD

የቴክኖሎጂ ሙከራው ተጠናቅቆ ሙሉ በሙሉ ሥራ ላይ በሚውልበት ሰዓት ቪክቶሪያ ውስጥ እያሽከረከሩ ሞባይል ሲጠቀሙ የተገኙ ሾፌሮች $496 ዶላርስና አራት የአሽከርካሪነት ነጥብ ቅነሳ፤ ኩዊንስላንድ ውስጥ $1000 ዶላርስና አራት የአሽከርካሪነት ነጥብ ቅነሳ መቀጮ ያገኛቸዋል።

አውስትራሊያ ውስጥ የሞባይል ስልኮች ተቆጣጣሪ ካሜራ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ቀዳሚ ኒው ሳውዝ ዌይልስ ስትሆን፤ ቴክኖሎጂውን በሥራ ላይ ካዋለች አምስት ወራት ተቆጥረዋል።

mobile phone detection
Source: Courtesy of PD

በተቀሩት የአውስትራሊያ ክፍለ አገራት አዲሱ የሞባይል ስልኮች ተቆጣጣሪ ካሜራ ቴክኖሎጂ ሥራ ላይ ባይውልም ሾፌሮች አውቶሞቢል እያሽከረከሩ ሞባይል ስልክ ሲጠቀሙ ከተገኙ መቀጮ ያገኛቸዋል።

የአውስትራሊያ ካፒታል ቴሪቶሪ፤ ሞባይል ስልክን በእጅ ይዞ መኪናን ማሽከርከር $480 ዶላርስና ሶስት የአሽከርካሪነት ነጥብ ቅነሳ መቀጮ - መኪና እየነዱ በሞባይል መልዕከት መለዋወጥ፣ ማኅበራዊ ግንኙነትን ማካሄድ፣ የሞባይል አፕ ወይም ኢንተርኔትን መጠቀም $589 ዶላርስና አራት የአሽከርካሪነት ነጥብ ቅነሳ መቀጮ ያስጥላል።

ደቡብ አውስትራሊያ፤ $534 ዶላርስና ሶስት የአሽከርካሪነት ነጥብ ቅነሳ መቀጮ

ምዕራብ አውስትራሊያ፤ $1000 ዶላርስና አራት የአሽከርካሪነት ነጥብ ቅነሳ መቀጮ

ኖርዘርን ቴሪቶሪ፤ $500 ዶላርስና ሶስት የአሽከርካሪነት ነጥብ ቅነሳ መቀጮ

ታዝማኒያ፤ $336 ዶላርስና ሶስት የአሽከርካሪነት ነጥብ ቅነሳ መቀጮን ያስከትላል።

 

 

  


2 min read

Published

By Kassahun Seboqa Negewo


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now