" የጆርጅ ፍሎይድ ህልፈተ ህይወት ሌሎችም ተነስተን የእስካሁኑ ይበቃል ከዚህ በላይ መሸከም አንችልም እንድንል የመጨረሻውን ግፊት አድርጓል ።" - ወጣት ሳሚ ኦባማ (ሳሚ ተስፋእዝጊ) “ መልእክቱ የፍትህ ጥያቄ ነው በስልጣን ላይ ያሉት ውሳኔ ሰጪዎች ድምጻችንን ሰምተው ለውጥ ካላመጡ እንደገና እዚሁ እንደምንገናኝ ያለምንም ጥርጥር እናረጋግጥላቸዋለን :: “ - ወጣት ዘነበች ተበጀ
“ብላክ ላይቭስ ማተር” በሚለው አለም አቀፍ መርህ ስር በአውስትራሊያ ባለፈው ቅዳሜ የነባር ህዝቦች ባዘጋጁት አገር አቀፍ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ተሳትፈዋል::
በሜልበርን በተደረገው ሰልፍ ላይ ከተሳተፉት ኢትዮጵያውያን አውስትራሊያውያን መካከል ወጣት ሳሚ ኦባማ (ሳሚ ተስፋእዝጊ ) እና ወጣት ዘነበች ተበጀን አነጋግረናል።
Share






