Watch FIFA World Cup 2026™

LIVE, FREE and EXCLUSIVE

የቀድሞዋ ቴኒስ ተጫዋች አሽ ባርቲ በናይዶክ ሳምንት የአመቱ ሰው ሽልማትን አሸነፈች

NAIDOC Ash Barty
This year's NAIDOC Awards' Person of the Year is Ash Barty (in photo with Cathy Freeman and Evonne Goolagong-Cawley during her last Australian Open win.) Source: Tennis Australia

ከተሸላሚዎቹ መካከል አሽ ባርቲ ፤ጃክ ቻርልስ እና በዲ ፍራንክሊን ይገኙባታል።


Published

Source: SBS


Share this with family and friends


ከተሸላሚዎቹ መካከል አሽ ባርቲ ፤ጃክ ቻርልስ እና በዲ ፍራንክሊን ይገኙባታል።


አመታዊው የናይዶክ ሳምንት ሽልማት በናርም (ሜልበርን) የተከናወነ ሲሆን በመግቢያውንም አክስት ጆይ  እንኳን ወደ አገራችን በሰላም መጣችህ የሚለውን ስነስርአት አከናውነዋል ።

“ ውብ ከሆነው የባህርዛፍ ጫፍ እስክ መሬት ስር ፤ ከእኛ ጋር ስትቀላቀሉ ፤ ለእኛ የሚያሳየን ነገር የቆምንበትን ይህንን ቀደምት መሬት ላበለት ቅድመ አያቶቻችንን መንፈስ ከበሬታን መስጠታችሁን ነው ። “

የኢንዲጅነስ ሚኒስትር ሊንዳ በርኒ በበኩላቸው በፌደራል መንግስት እና ቀደምት ነዋሪዎች መከከል ስምምነት እንደሚፈጸም ተናግረዋል ።

" ሁላችንም ይህችን አገር መቀየር ይኖርብናል ፤ ይህችን አገር እንቀይራለን፤ ምክንያቱም ቀኑ መጥቷልና።" 

የናይዶክ ሳምንት ተሸላሚ ከሆኑት መካከል አጎት ጃክ ቻርልስ፤ የጠፉት ትውልዶች ተብለው ለሚታወቁት ቀሪ ዜጎች ላበረከቱት አስተዋጥጸኦ ፤ የአረጋዊ ወንድ ሽልማትንን ወስደዋል።

 የቀድሞዋ ቴኒስ ተጫዋች አሽ ባርቲ የአመቱ ሰው በመባል የተሰየመች ሲሆን ፤ የ26 አመቷ አሽ ባርቲ ከአገር ውጭ በመሆኗም ሽልማቷን አባቷ በእሷ ስም ተቀብለዋል ።

ከዚህ በተጨማሪም የአውስትራሊያ ፉትቦል የሲድኒ ስዋን ተጫዋች የሆነው ጃክ ቻርልስ፤ የስፖርት ሰው ሽልማትን ተቀብሏል ።

ናይዶክ ሳምንት እስክ ጁላይ 10 ደርስ ይቀጥላል ። (የጀመረው በጁላይ 3 ነው )


Latest podcast episodes

Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Stream now