Facing Justice: Eshetu Alemu

Facing Justice: Eshetu Alemu

Source: Courtesy of Public, KA, KM, and SA

የቀድሞው የደርግ አባልና የጎጃም ክፍለ ሃገር ተጠሪ የነበሩት እሸቱ ዓለሙ ወጣቶችን አለአግባብ ለእሥራትና ለስቃይ ዳርገዋል፣ ሲልም ለሕልፈተ ሕይወት አብቅተዋል በሚል ወንጀል ተጠርጥረው ዘ-ሄግ ኔዘርላንድስ ውስጥ ክሳቸው በአንድ ፍርድ ቤት እየታየ ነው። ብይኑም በወርኃ ዲሴምበር አጋማሽ ላይ ይተላለፋል ተብሎ ይጠበቃል። ጋዜጠኛ ክንፉ አሰፋ የክሱን አነሳስና ምስረታ ሂደት አስመልክቶ፣ ከሰለባዎቹ አንዱ የሆኑት አቶ ቁምላቸው መኩሪያ በእሳቸውና በጓደኞቻችቸው ላይ በወቅቱ ስለደረሱት እሥራት፣ ግርፋትና ግድያዎችን በተመለከተ ጉዳዩን ለያዙት የኔዘርላንድስ የሕግ ባለሙያዎች ከሰጡት የምስከር ቃል አጣቅሰው፤ እንዲሁም የፍርዱን ሂደት በቅርበት ያላማቋረጥ የተከታተሉት አቶ ሲራክ አሰፋው በዓቃቤ ሕግ፣ በተከሳሽና የመከላከያ ጠበቆች አማካይነት የቀረቡ ማስረጃዎችንና ክርክሮችን ነቅሰው ይናገራሉ።



Share

Follow SBS Amharic

Download our apps

Listen to our podcasts

Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now