የሁለቱን ሲኖዶሶች ውህደት ምክንያት በማድረግ በአውስትራሊያ ሜልበርን ታላቅ የእርቅና የአንድነት ጉባኤ ሴፕቴምበር 29,2018 ተደርጓል። በጉባኤ በአውስትራሊያ የኢፊዴሪ ባለ ሙሉ ባለ ሰልጣን አምባሳደር ትርፉ ኪዳነማርያም እና የኢምባሲው ማህበረሰብ የየሀገረ ስብከቱ እና ደብሩ የሃይማኖት አባቶች መዘምራንና ምእመናን ተገኝተው ነበር ። ብጹእ አቡነ ሔኖክ በጉባኤው መክፈቻ የቤተክርስቲያኒቱን ጥንታው ታሪክ አንስተው የተናገሩ ሲሆን ብጹእ አቡነ ጴጥሮስ በበኩላቸው ቤተክርስቲያኒቱን ከዚህ በኋላ ለአገር ግንባታ የቆመች መሆኗን አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ መንግስት እያራመደው ባለው ለውጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የምታበረክተው አስተዋጻኦ ከፍተኛ መሆኑና በቀጣይም ኢምባሲው ከኢትዮጵያውያን አውስትራሊያውያን ጋር ባንድነት እንደሚሰራ አምባሳደር ትርፉ ኪዳነማርያም ቃል ገበተዋል። የጉባኤውንም አጠቃይ ይዘትና ያመጣውንም ፋይዳ አስመልክተንም ከብጹእ አቡነ ጴጥሮስ በአውስትራሊያና ኒውዚላንድ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና በአውስትራሊያ የኢፊዴሪ ባለ ሙሉ ባለ ሰልጣን አምባሳደር ትርፉ ኪዳነማርያም ጋር ቆይታ አድርገናል።
Share






