በቅርቡ በሀገረ አሜሪካ - ኦክላሃማ ዩኒቨርሲቲ፤ የአንጋፋው ኢትዮጵያዊ ሰዓሊና ገጣሚ ገብረክርስቶስ ደስታ የጥበብ ሥራዎችና የሕይወት ዘመን አሻራዎቹ ላይ ያተኮረና የዘከረ ሲፖዚየም ተካሂዷል። የሕይወት ዘመን የጥበብ ሥራዎቹን አንስተው ከዘከሩት ተጠባቢዎች መካከል በሥነ ግጥም፣ ሥነ ቀለም ቅብ፣ ቅርፃ ቅርፅና የንድፍ ሥራዎች ዘርፍ ስመጥርና መምህርት የሆኑት ከበደች ተክለአብ ናቸው።
በበርካታ ፅሑፎች ገብረ ክርስቶስ ደስታን የአውሮፓ ውጤት ብቻ አድርገው ያቀርባሉ። በተለይም ስዕሎቹን በሚመለከት የጀርመን expressionism ዝንባሌው በብዛት ተፅፏል። በእርግጥም፤ የጀርመን expressionism ዝንባሌ አለበት። በእኔ ጥናትና አስተሳሰብ ያ ብቻ ሳይሆን የpure abstraction ዝንባሌም የነበረውና ከእዚያም በላይ የሔደ ሰው ነው። በእዚያ ዘመናዊነት ውስጥ ኢትዮጵያዊ ሥራም አለበት።ከበደች ተክለአብ
Share






