Public forum in Canberra to support Ethiopia’s Prime Minister Dr Abiy Ahmed

. Source: Supplied
የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ወደ ኃላፊነት ከመጡ በኋላ ላመጧቸው ለውጦች ድጋፍ እና እውቅና ለመስጠት በካንብራ የተጠራ የውይይት መድረክ። ቅዳሜ ሴፕቴምበር 8, 2018 በአውስትራልያ ዋና ከተማ ካንብራ በኢትዮጵያ የተከሰተውን ለውጥ ለመደገፍ “ የመደመርና የመቀራረብ ውይይት ተደርጎ ነበር። በውይይቱም በአውስትራሊያ የኢፊድሪ ባለሙሉ ስለጣን አምባሳደር ትርፉ ኪዳነማርያምና በካንብራ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ተሳትፈዋል። የኢምባሲው ማህበረሰብም ከአብላጫው የካንብራ ነዋሪዎች ጋር ተገናኝተው ሲወያዩ ይህ የመጀመሪያው እንደሆነ አዘጋጅ ኮሚቴዎቹና ተሳታፊዎቹ ገልጸዋል። እኛም ወይይቱን አስመልክትን ከዶ/ር ሸሪፍ ሰይድ በካምብራ "የመደመርና የመቀራረብ ውይይት" ዝግጅት ሰብሳቢ እና አወያይ ፤ወ/ሪት ስንታየሁ ፍቅሬ የዝግጅቱ ኮሚቴ አባል ፤ ወ/ሮ አዱኛ አለሙ የዝግጅቱ ተሳታፊ ፤ አቶ ከፍያለው አዲስ ጋር ቆይታ አድርገናል።
Share




