አንኳሮች
- በዓለ ጥምቀት በብሪስበን
- ማኅበራዊ ፋይዳዎች
- መንፈሳዊና ማኅበረሰባዊ አንድነት
- የበዓል ከበሬታ ጥሪ
ጥምቀት ከኢትዮጵያዊ በዓልነት አልፎ ወደ ዓለም አቀፋዊ በዓልነት አድጓል። ይህ ደግሞ ለቤተ ክርስቲያናችንም፣ ለሀገራችንም ትልቅ አንድምታ ያለው ነው።ቀሲስ መልአከ ፀሐይ መንግሥቱ ኃይሉ
ጥምቀት በብዙ ሀገሮች ይከበራል፤ ነገር ግን እንደ ኢትዮጵያ ደምቆ የሚከበርበት፣ ባሕር ወርዶ አድሮ የሚከበርበት፣ ታቦታቱ ወርደው፣ ወንዝ አድረው ፤ ካህናቱ፣ ጳጳሳቱ፣ እላይ ቅዱስ ፓትሪያርኩ ድረስ ወርደው አክብረው፣ ባርከው የሚመለሱበት ሁኔታ የለም። ይህ ነገር ብዙዎችን እያስገረመ፣ ብዙዎችን እየማረከ፣ ብዙዎች ወደ እዚያ እንዲሔዱ እያነሳሳ ለሀገሪቱም ትልቅ ጥቅም ያመጣል። ለቤተ ክርስቲያኒቱም ትልቅ ሀብት ነው።ቀሲስ መልአከ ፀሐይ መንግሥቱ ኃይሉ
ዘንድሮ ብሪስበን ውስጥ የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያንና የቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ለመጀመሪያ ጊዜ አብረው ሆነው ነው በዓሉን የሚያሳልፉት። ጥሩ በዓል እንደምናሳልፍ ምንም ጥርጥር የለውም።ቀሲስ መልአከ ፀሐይ መንግሥቱ ኃይሉ
የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን ወደ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን እየሔዱ፤ የቅዱስ ገብርኤልም ወደ ቅዱስ ጊዮርጊስ እየመጡ መንፈሳዊ አገልግሎቱን ሊካፈሉ የሚችሉበት ትልቅ መድረክ ነው የተከፈተው። ወደ ፍቅር፣ ወደ ጥሩ መንገድ እያመራን ነው።አቶ ወርቅነህ ባየህ
ዘንድሮ ሁለት ነን። አንድ አዲስ የተተከለ ቤተ ክርስቲያን አለ፤ ቅዱስ ሚካኤል። በቀጣዩ ዓመት እሱንም ይዘን አብረን እንወጣለን።ቀሲስ መልአከ ፀሐይ መንግሥቱ ኃይሉ





