ቃለ ምልልስ - አቶ ሀይለ ልኡል ገብረ ሰላሴ በዘንድሮው የአውስትራሊያ ቀን "ኦርደር ኦፍ አውስትራሊያ" የክብር ሽልማት ተሸላሚ

.

Ato Haileluel Gebreselassie Source: SBS Amharic

አቶ ሀይለ ልኡል ገብረ ስላሴ የአፍሪክውያን ቲንክ ታንክ መስራች አባል እና የወቅቱ ሊቀመንበር አንዲሁም በቪክቶርያ ፖሊስ የአፍሪካውያን ግብረ ሃይል ሰብሳቢ ፤ በዘንድሮው የአውስትራሊያ ቀን ፤የኦርደር ኦፍ አውስትራሊያ የክብር ሽልማት ተሸላሚ ሆነዋል።የዚህን ሽልማት ሂደት የአውስትራሊያ የአገረ ገዥ መስሪያ ቤት የሚመራው ሲሆን ፡በየጊዜውም ከተለያዩ ቦታዎች የሚደርሱትን ጥቆማዎች በማጣራት እና የእማኞችን የድጋፍ ግባት በመመዘን ተገቢ ለሆኑ እጩዎች ሽልማቱን ያበረክታል። አቶ ሀይለ ልኡል ባለፉት ፪፭ አመታት በአውስትራሊያ ለቪክቶሪያውያን ማህበረሰብ አባለት እንዲሁም በአገር አቀፍ ደርጃ ከመንገስት ጋር ፤ በበጎ ፈቃደኝነት እና በመደበኛው ስራቸው ያበረከቱዋቸው አስተዋጻኦዎች ተመዝነው ለዚህ ታላቅ የክብር ሽልማት እንዳበቃቸው ነገረውናል። ይህ ሽልማት ተጨማሪ ሃላፊነቶችንም እንዲቀበሉ እና ማህበረሰቡንም ለማገልገል የበለጠ እንዲተጉ እንደሚያደርጋቸው ገልጸዋል።



Share
Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service