በዓለ ትንሣኤ በኢትዮጵያውያንና በዓለም የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ዘንድ እየተከበረ ነው

*** በአውስትራሊያውያን ዘንድም በየአብያተ ክርስቲያናቱ በድምቀት ተከብሯል

Community

Ethiopian Christians living in Australia take part in the Resurrection Mass at Medhanialem Ethiopian Orthodox Church in Melbourne on April 23, 2022. Source: SBS Amharic

ዛሬ እሑድ ኤፕሪል 24 በመላው ዓለም በዓለ ፋሲካ እየተከበረ ይገኛል። 

ኢትዮጵያ ውስጥም በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በሙሉ በዓለ ትንሣኤው በድምቀት ተከባሪ ነው።

በዓሉን አስመልክቶም የሃይማኖት መሪዎች በዋዜማው የእንኳን አደረሳችሁ መንፈሳዊ መልዕክቶቻቸውን ለሕዝበ ክርስቲያኑ አስተላልፈዋል። 

የበዓሉንም ዋነኛ ዕሳቤ አስመልክተው “የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ የሰው ልጅ ኃጢአት የተሰረየበት ፣ ፍቅር የተገኘበትና መድኅን የተጎናፀፈበት ነው” ሲሉ አስገንዝበዋል።

 

ሕዝበ ክርስቲያኑ ዕለተ ፋሲካን በሐሴት ሲያከብር ለጉስቁልና የተጋለጡ፣ ለእርዛት የተዳረጉትንም በችሮታቸው በመጎብኘት ሊሆን እንደሚገባ አሳስበዋል። 

 

ኢትዮጵያ ውስጥ ተከስቶ ያለው የስላም መደፍረስም ሕዝባዊ ጥረቶች ታክለውበት አስቸኳይ እልባት እንዲበጅለት ጥሪ አቅርበዋል። 
News
Residents at Kalyna aged care centre attending orthodox Easter service. Source: SBS
በአገረ አውስትራሊያም ኢትዮጵያውያን የክርስትና እምነት ተከታዮችን ጨምሮ በኦርቶዶክስ ሃይማኖት አማኞች ዘንድ ከአረጋውያን ክብካቤ ማዕከላት እስከ አብያተ ክርስቲያናት ተከብሯል።  


Share

Published

By Kassahun Seboqa Negewo

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
በዓለ ትንሣኤ በኢትዮጵያውያንና በዓለም የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ዘንድ እየተከበረ ነው | SBS Amharic