SKIP TO MAIN CONTENT

በዓለ ትንሣኤ በኢትዮጵያውያንና በዓለም የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ዘንድ እየተከበረ ነው

*** በአውስትራሊያውያን ዘንድም በየአብያተ ክርስቲያናቱ በድምቀት ተከብሯል

Community
Ethiopian Christians living in Australia take part in the Resurrection Mass at Medhanialem Ethiopian Orthodox Church in Melbourne on April 23, 2022. Source: SBS Amharic

1 min read

Published

By Kassahun Seboqa Negewo


Skip to article content

ዛሬ እሑድ ኤፕሪል 24 በመላው ዓለም በዓለ ፋሲካ እየተከበረ ይገኛል። 

ኢትዮጵያ ውስጥም በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በሙሉ በዓለ ትንሣኤው በድምቀት ተከባሪ ነው።

በዓሉን አስመልክቶም የሃይማኖት መሪዎች በዋዜማው የእንኳን አደረሳችሁ መንፈሳዊ መልዕክቶቻቸውን ለሕዝበ ክርስቲያኑ አስተላልፈዋል። 

የበዓሉንም ዋነኛ ዕሳቤ አስመልክተው “የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ የሰው ልጅ ኃጢአት የተሰረየበት ፣ ፍቅር የተገኘበትና መድኅን የተጎናፀፈበት ነው” ሲሉ አስገንዝበዋል።

 

ሕዝበ ክርስቲያኑ ዕለተ ፋሲካን በሐሴት ሲያከብር ለጉስቁልና የተጋለጡ፣ ለእርዛት የተዳረጉትንም በችሮታቸው በመጎብኘት ሊሆን እንደሚገባ አሳስበዋል። 

 

ኢትዮጵያ ውስጥ ተከስቶ ያለው የስላም መደፍረስም ሕዝባዊ ጥረቶች ታክለውበት አስቸኳይ እልባት እንዲበጅለት ጥሪ አቅርበዋል። 

News
Residents at Kalyna aged care centre attending orthodox Easter service. Source: SBS

በአገረ አውስትራሊያም ኢትዮጵያውያን የክርስትና እምነት ተከታዮችን ጨምሮ በኦርቶዶክስ ሃይማኖት አማኞች ዘንድ ከአረጋውያን ክብካቤ ማዕከላት እስከ አብያተ ክርስቲያናት ተከብሯል።  


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Stream now