ሲድኒ ላይ የፊት ጭምብል ማጥለቅ ግዴታ በከፊል ተጣለ

*** ቪክቶሪያ ውስጥ በኮሮናቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 32 ደረሰ

Amharic News 03 January 2021

Source: AAP

ኒው ሳውዝ ዌይልስ በኮሮናቫይረስ ማገርሸት ሳቢያ በተወሰኑ ሥፍራዎች የፊት ጭምብል የማጥለቅ ግዴታን ጣለች።

በዚህም መሠረት፦

  • የገበያ ማዕከላት
  • ሲኒማዎች
  • የእምነት ቤቶች
  • የፀጉርና የቁንጅና ሳሎኖች
  • የጌም መጫዎቻዎች
  • የሕዝብ ትራንስፖርትና
  • የመዝናኛ ሥፍራ ሠራተኞች
የፊት ጭምብል የማድረግ ግዴታ ተጥሎባቸዋል።

የኒው ሳውዝ ዌይልስ ፕሪሚየር ግላዲስ በርጂክሊያን ሲድኒ ትላልቅ ኩነቶችን ለማተናገድ ተሰናድታ ባለችበትና ሠራተኞችም ወደ መደበኛ የሥራ ገበታቸው በሚመለሱበት ወቅት የፊት ጭምብል የማድረግ ግዴታን የመጣሉ ወቅታዊነት ተገቢ ጊዜ ላይ መሆኑንና ከእኩለ ለሊት ጀምሮም ግብር ላይ እንደሚውል ተናግረዋል። 

የኒው ሳውዝ ዌይልስ መንግሥት የፊት ጭምብል የማድረግ ድንጋጌን እንዲያሳልፍ ከጤና ባለ ሙያዎች ብርቱ ግፊት የደረሰበት ሲሆን ከአውስትራሊያ የሕክምና ባለ ሙያዎች ማኅበር በኩልም በፍጥነት ገደቦችን ባለመጣል ብርቱ ትችት ተሰንዝሮበታል። 

ቪክቶሪያ

ቪክቶሪያ ባለፉት 24 ሰዓታት ሶሶት ሰዎች በኮሮናቫይረስ መጠቃታቸውን አስመዘገበች።

ይህም በጠቅላላው ቪክቶሪያ ውስጥ በቫይረሱ የተጠቁትን ሰዎች ቁጥር 32 አድርሷል። 

የቪክቶሪያ ኮቨድ-19 ምርመራ ፕሮግራም አዛዥ ጄሮን ዌይማር የቪክቶሪያ ነዋሪዎች ቫይረሱ የተገኘባቸውን ሥፍራዎች ለማወቅ የቪክቶሪያ ጤና ድረ-ገጽን እንዲጎበኙ አመላክተዋል።  

 

 

 

 


Share

Published

By NACA
Presented by Kassahun Seboqa Negewo

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service