በርካታ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ያሳፈረች ጀልባ ሰጥማ ከ 68 በላይ የሚሆኑት ሕይወታቸው ተቀጠፈ

የተባበሩት መንግሥታት የፍልሰተኞች ድርጅት ( IOM ) እንዳስታወቀው ኢትዮጵያውያኑ ሕይወታቸውን ያጡት በየመን አብያን ግዛት ነው።

gettyimages-2213915817-612x612.jpg

The International Organisation for Migration (IOM) of the United Nations (UN). Photo: Credit: Christiane Oelrich/picture alliance via Getty Images)

የተመድ የፍልሰተኞች ድርጅት እንዳለው በርካቶችን ወደ ሳዑዲ ዓረቢያ ድንበር ለማድረስ ጭና ስትጓዝ የነበረችው ጀልባ በመስጠሟ ከ 68 በላይ ስደተኞች ሕይወታቸው ተቀጥፏል፤ 74 ስደተኞች የደረሱበት አልታወቀም።

ሕይወታቸው ካለፈው ውስጥ አብዛኞቹ ኢትዮጵያውያን ናቸውም ብሏል።

አሶሽዬትድ ፕሬስ የ54ቱ ስደተኞች አስከሬን በባሕር ዳርቻ በአሳዛኝ ሁኔታ ወዳድቆ ነው የተገኘው።

የፍልሰተኞቹ ድርጅት እስካሁን 12 ሰዎች በሕይወት ተርፈው መገኘታቸውን ገልፆ፤ ሌሎች አስከሬኖችን እና በሕይወት የተረፉ ካሉ ለማግኘት ፍለጋው ይቀጥላል ብሏል።


1 min read

Published

By Stringer Report

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now