ኢትዮጵያ ውስጥ የተከሰቱ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች ቀጣይ ምርመራ እንደሚያሻቸው የተመድ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ገለጠ

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ሕይወታቸው ያለፈ ተዋጊዎችን ለመዘከር ለሶስት ቀናት የሚቆይ የሐዘን ቀናትን መሰየሙን አመለከተ

SBS Amharic News Podcast Radio Telescopes.jfif

Credit: SBS Amharic

የተባበሩት መንግሥታት ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን የኢትዮጵያ ጉዳዮች ተጠባቢ ቡድን በእጅጉ አሳሳቢ የሆኑ የኢትዮጵያን ሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች በገለልተኛ መርማሪዎች የሚካሔድ ምርመራን መቀጠል አስፈላጊ መሆኑን አሳሰበ።

የኮሚሽኑ ሰብሳቢ፤ መሐመድ ቻንዴ ኦትማን ሪፖርቶች እንደሚያመለክቱት ከሆነ በመፈፀም ላይ ብርቱ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች፣ መጠነ ሰፊ አመፅና አለመረጋጋት ለመፃዒ አስከፊ የወንጀል ተግባራትና ከተጠያቂነት ማምለጥ አስባብ እንደሚሆኑ አመላክተው፤ ባለፈው ወር የኮሚሽናቸው ሪፖርት ውስጥም ኢትዮጵያ ውስጥ ከኖቬምበር 3 ቀን 2020 አንስቶ የጦር ወንጀሎችና ሰብዓዊ ወንጀሎች ስለ መፈፀማቸው ከድምዳሜ ላይ የደረሰ መሆኑን አስታውቀዋል።

ከሰሜን ኢትዮጵያ የኖቬምበር 2022 የተኩስ አቁም ስምምነት ወዲህም የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች መካሔዳቸውም የተመለከተ ሲሆን፤ በብርቱ ወንጀልነት የሚጠቀሱ በሰብዓዊ ፍጡር ላይ የተፈፀሙ ወንጀሎች መካሔዳቸውም ተጠቅሷል።

በተያያዥነትም የኤርትራ ጦር ኢትዮጵያ ውስጥ መኖርና በተለይም የፆታ ጥቃቶች መፈፀም ያልተቋረጠ መሆኑን፤ እንዲሁም በአማራ ክልል ከሕግ / ፍርድ ቤት ብይን ውጪ የሚካሔዱ ግድያዎች፣ የጅምላ እሥራት መካሔድንና ተገቢ ምላሾች ነፈጋዎችን የሚያመለክቱ ሪፖርቶች እየቀረቡ መሆኑን አመላክቷል።

የሐዘን ቀናት

በሰሜን ኢትዮጵያ በተካሔደው ጦርነት ሳቢያ ሕይወታቸው ያለፈ የሕወሓት ተዋጊዎችን ለቤተሰቦቻቸው ሥርዓተ ሐዘንን ጠብቆ ለማርዳትና ዝክረ መታሰቢያም ለማድረግ ከኦክቶበር 13 / ጥቅምት 2 አንስቶ ለሶስት ቀናት እንደሚካሔድ ተነግሯል።

በዝክረ መታሰቢያው የመጀመሪያ ዕለትም ሕይወታቸውን ያጡ ተዋጊ አባላት ስም ዝርዝር በይፋ እንደሚነገር የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዚደንት ጄኔራል ታደሰ ወረደ አስታውቀዋል።

Share

Published

By Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
ኢትዮጵያ ውስጥ የተከሰቱ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች ቀጣይ ምርመራ እንደሚያሻቸው የተመድ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ገለጠ | SBS Amharic