የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ከኃላፊነታቸው ለቀቁ

ከሰባት ዓመታት በላይ በተለያዩ ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊነት ሥፍራዎችና የብሔራዊ ባንክ ገዢ ሆነው ያገለገሉት አቶ ማሞ ምህረቱ በገዛ ፈቃዳቸው ከኃላፊነታቸው መልቀቃቸውን ይፋ አደረጉ፡፡

Mamo.png

Mamo Miheretu, the outgoing National Bank of Ethiopia (NBE) Governor. Credit: NBE

ማሞ ምህረቱ ቀደም ሲል የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆሊዲንግስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ፣ እንዲሁም የጠቅላይ ሚኒስትሩ ከፍተኛ የምጣኔ ሀብት አማካሪና የንግድ ጉዳዮች ተደራዳሪ የነበሩ ሲሆን፤ ቀደም ሲልም በዓለም ባንክ ውስጥ በከፍተኛ ባለሙያነት አገልግለዋል።

 ከጥር 10 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ነሐሴ 28 ቀን 2017 በብሔራዊ ባንክ ገዢነት ያገለገሉት ማሞ ምህረቱ በገዛ ፈቃዳቸው ከኃላፊነት መልቀቃቸውን ይፋ ያደረጉት በኤክስ የማኅበራዊ ትስስር ገፃቸው ነው።

አቶ ማሞ፤ በምስጋናና ስንብት መልዕክታቸው ለብሔራዊ ባንክ ገዢነት ይሁንታቸውን የቸሯቸውንና ለሥራቸውም ስኬት ድጋፋቸውን እንደለገሷቸው የጠቀሷቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን አመስግነዋል።

ባለፉት 50 ዓመታት ባልታየ መልኩ በእጅጉ ብርቱ የሆነ የሀገር በቀል ምጣኔ ሃብት ፕሮግራም ላይ ከቀረፃ እስከ ትገበራ የአመራር አሻራቸው ያለበት መሆኑን አንስተዋል።

ተሰናባቹ የብሔራዊ ባንክ ገዢ፤ አክለውም በፋይናንስ መስክ የውጭ ባንክ አገልግሎቶችን፣ የዘመነ የዲጂታል ኣካታችን እንዲከፍት ማስቻላቸውን፣ ሲልም፤ የዓለም ገንዘብ ድርጅትና የዓለም ባንክን ከመሰሉ የውጭ የፋይናንስ ሽርካዎች 10 ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር ማስገኘታቸውን፣ በእሳቸው አመራር ወቅትም የዋጋ ግሽበት ዝቅ ማለቱንና የዲጂታል ክፍያ ከፍ ለማለት መብቃቱን በአንኳርነት ነቅሰው አመላክተዋል።
የአቶ ማሞን ስንብት ተከትሎም፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ነሐሴ 28 ባወጣው መግለጫ፤

"የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ክቡር ገዢ አቶ ማሞ ምሕረቱ በስራ ዘመናቸው ላበረከቱት ልዩ አመራርና ላሳዩት የአገልግሎት ቁርጠኝነት ልባዊ ምስጋናው ይገልፃል። ክቡር ገዢው በአገልግሎት ላይ በነበሩበት ወቅት ከሌሎች የሥራ ባልደረቦቻቸው ጋር ለበርካታ ዓመታት ሲጠበቁ የነበሩ የማክሮ ኢኮኖሚክ ሪፎርሞችን ተግባራዊ አድርገዋል።

"የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ክቡር ገዢ አቶ ማሞ ምሕረቱ ላሳዩት ከፍተኛ የሆነ የአመራር ጥበብ እና ቁርጠኝነት የተሰማውን ጥልቅ ምስጋና እየገለጸ የወደፊት የስራ ዘመናቸው ስኬታማ እንዲሆን ልባዊ ምኞቱን ይገልጻል" ብሏል።

ተሰናባቹ የባንክ ገዢ በማን እንደሚተኩ እስካሁን በይፋ አልተነገረም።

Share

Published

Updated

By Stringer Report
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ከኃላፊነታቸው ለቀቁ | SBS Amharic