ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ አገር ቤት እንዳይገቡ ተከለከሉ

ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ወደ ዩናይትድ ስቴትስ ማቅናታቸው ተመልክቷል።

Abune Petros AUST.jpg

His Eminence Abune Petros, General Secretary of the Holy Synod and Archbishop of the Diocese of New York and surrounding areas. Credit: SBS Amharic

ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የቅዱስ ሲኖዶስ ፀሐፊ፣ የኒውዮርክና አካባቢው ሊቀ ጳጳስ፤ ወደ አገር ቤት እንዳይገቡ ከአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማለፊያ እንዲመለሱ መደረጉ ተመልክቷል።

የብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ወደ አገር መግባት መከልከል ይፋ ያደረገው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሲሆን፤ የእገዳው አስባብ ምን እንደሆነ ግና አክሎ አልተገለጠም።

በሌላም በኩል አግባብ ባላቸው የኢትዮጵያ መንግሥት ባለስልጣናት በኩል የቅዱስ ሲኖዶስ ከፍተኛ አመራር አባሉን ከአውሮፕላን ማረፊያ እንዳያልፉ መታገድ አስመልክቶ እስካሁን ጉዳዪን አስመልክቶ ማስተባበያም ሆነ ማረጋገጫ አልተሰጠም።

ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ወደ ዩናይድ ስቴትስ የሔዱት የጥምቀት በዓል ላይ መገኘትና የመንፈስ ልጆቻቸውን መጎብኘትን አክሎ፤ ሐዋሪያ ተግባራቸውን ለመፈፀም እንደሆነም በቤተክርስቲያኒቱ የሕዝብ ግንኙነት በኩል ተነግሯል።

Share

Published

Updated

By Stringer Report
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service