ኢሰመኮ በሆሮ ጉዱሩ የተፈፀመው ጥቃት ያሳዘነውና ያሳሰበው መሆኑን ገለጠ

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ጳጉሜን 1 ይፋ ባደረገው መግለጫ በኦሮሚያ ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን በምትገኘው ኡኑሩ ወረዳ በርካታ ሰዎች መገደላቸውን፣ መቁሰላቸውንና በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎች መፈናቀላቸውን አስታውቋል።

Horo Guduru

Horo Guduru. Credit: EHRC

ኮሚሽኑ እንዳስታወቀው ነሐሴ 23 እስከ ነሐሴ 24, 2014 በታጣቂዎች በተፈፀሙ ጥቃቶች በርካታ ሰዎች ተገድለዋል፣ ቆስለዋል፣ እንዲሁም ከ20ሺህ በላይ ሰዎች ከቀዬአቸው ተፈናቅለው ወደ ኦቦራ ከተማ ፈልሰዋል።

የኮሚሽኑ መግለጫ አክሎም፤ "በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን ኡሙሩ ወረዳ አገምሳ ቀበሌ የኦሮሞ ነትጻነት ሠራዊት (በተለምዶ "ኦነግ ሸኔ" ተብሎ የሚጠራ) ታጣቂዎች የወረዳው ዋና ከተማ የሆነችውን ኦቦራ ከተማን ለመያዝ ባደረጉት እንቅስቃሴ ሦስት የአማራ ብሔር ተወላጆች መግደላቸውን ተከትሎ ከኡሙሩ ወረዳ፣ ህሮ አዲስ ዓለም ከተባለ ቀበሌና አጎራባች ከሚገኘው የአማራ ክልል፣ ቡሬ ወረዳ የተወጣጡ ታጣቂዎች በኡሙሩ ወረዳ በሚገኙና አገምሳ፣ ጆግ ምግር፣ ታም ኢላሙ፣ ጀቦ ዶባን፣ ጦምቤ ዳነጋበ፣ ጃውጅ፣ ኛሬ፣ ለገ ሚቻ፣ ሉቁማ ዋሌ በሚባሉ ቀበሌዎች የኦሮሞ ብሔር ተወላጅ ነዋሪዎች ላይ ነሐሴ 24 እና 25 ቀን 2014 ጥቃት ፈጽመዋል" ብሏል።

በሁለቱ ቀናት በተካሔዱት ጥቃቶች ሳቢያም ከ60 በላይ ሰዎች ሲገደሉ፤ ከ70 በላይ ሰዎች መቁሰላቸውን፣ የነዋሪ ቤቶችና የቀንድ ከብቶች መዘረፋቸውን ኮሚሽኑ ካነጋገራቸው የአካባቢው ነዋሪዎች የተረዳ መሆኑንም ገልጧል።

በዞኑ ውስጥ ባሉ ሌሎች ወረዳዎችም ጥቃቶች መድረሳቸውንና የፀጥታና ደኅነት ስጋቶች ሰፍነው ያሉ መሆኑን የኮሚሽኑ መግለጫ አያይዞ ያመለከተ ሲሆን፤ የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለም በበኩላቸው በደረሱት ጥቃቶች ማዘናቸውንና ሁነቱ ያሳሳባቸው መሆኑን ተናግረዋል።


Share

Published

By Stringer Report
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
ኢሰመኮ በሆሮ ጉዱሩ የተፈፀመው ጥቃት ያሳዘነውና ያሳሰበው መሆኑን ገለጠ | SBS Amharic