የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ተጀመረ

በጉባኤው አፍሪካ በአየር ንብረት ለውጥ የተነሳ እየገጠሟት የሚገኙ አንገብጋቢ ፈተናዎችን በዘላቂነት መሻገር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር ይደረጋል፡፡

gettyimages-2233740232-612x612.jpg

Djibouti's President Ismail Omar Guelleh (3rd L), Ethiopia's Prime Minister Abiy Ahmed (4th L), Kenya's President William Ruto (4th R) and African Union Commission Chairperson Mahmoud Ali Youssouf (3rd R) pose for a group photo with other African heads of state and government representatives during the opening of the High-Level Leaders Summit at the Second Africa Climate Summit (ACS2) in Addis Ababa, on September 8, 2025. Credit: LUIS TATO/AFP via Getty Images

ከጳጉሜ 3 እስከ ጳጉሜ 5 ቀን 2017 ዓ.ም የሚካሄደው 2ኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ ዛሬ በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በይፋ ተከፍቷል።

“ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መፍትሄዎችን ማሳለጥ፣ የአፍሪካን አረንጓዴ ልማት በፋይናንስ መደገፍ” በሚል መሪ ሀሳብ የሚካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ አፍሪካ እየገጠሟት የሚገኙ አንገብጋቢ ፈተናዎችን በዘላቂነት መሻገር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር እንደሚደረግበት ተገልጿል።

አፍሪካውያን ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መፍትሄዎችን የሚመክሩበትና የአፍሪካን አረንጓዴ ልማት የሚደገፍበትን አማራጭ የሚያጤኑበት እንደሚሆንም ይጠበቃል።

ጉባኤው በዋናነት በሁለት አጀንዳዎች ላይ መሰረት አድርጎ እንደሚካሄድ የተገለጸ ሲሆን፤ በቅድሚያ የአፍሪካን የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳት መሰረት ያደረጉ አህጉራዊ መፍትሄዎች ዕውቅና ይሰጣቸዋል ተብሏል፡፡
gettyimages-2233742556-612x612.jpg
The logo of the Second Africa Climate Summit (ACS2) is displayed at the entrance to the plenary hall during the opening of the High-Level Leaders Summit in Addis Ababa, on September 8, 2025. Credit: LUIS TATO/AFP via Getty Images
ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ፋይናንስም በጉባኤው ተከታዩ አጀንዳ እንደሚሆን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል፡፡

በጉባኤው ኢትዮጵያም የአየር ንብረት ለውጥ ችግርን በጋራ መከላከል የተሻለ ውጤት ለማምጣት ያላትን አቋም እና ያከናወነቻቸውን ተግባራት በጉባኤው ታንፀባርቃለች ተብሎ ይጠበቃል።

በመድረኩም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ፣ የአህጉር አቀፍ የራስ መተማመን፣ አንድነትና የንፁህ ኢነርጂ ምልክት ነው ያሉ ሲሆን፤ ይህ ግድብ ከኢትዮጵያ ባሻገር ለምስራቅ አፍሪካ ከ5 ሺህ ሜጋ ዋት በላይ ታዳሽ ሃይል እንደሚያመነጭ ጠቁመዋል።

እኛ እዚህ የመጣነው የዓለምን ቀጣይ የአየር ንብረት ኢኮኖሚ ለመንደፍ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ አፍሪካ ስነ ምህዳሯን ሳታጠፋ በኢንዱስትሪው ዘርፍ ፈጣን እድገት ያስመዘገበች የመጀመሪያዋ አህጉር ልትሆን እንደምትችል ተናግረዋል።

ማክሰኞ ጳጉሜን 4 ቀን 2017 የተመረቀው የሕዳሴው ግድብ ከ 3 ሚሊዮን የሚልቁ የህብረተሰብ ክፍሎችን በጭስ ከተሞሉ ኩሽናዎችና የእናቶችንና ሴቶች የእለት ተእለት ሸክሞችን እንደሚያቀል ገልጸዋል።
gettyimages-2233897119-612x612.jpg
Prime Minister of Ethiopia Abiy Ahmed delivers his remarks during the official inauguration ceremony of the Grand Ethiopian Renaissance Dam (GERD) in Guba, on September 9, 2025. Ethiopia inaugurated the continent's largest hydroelectric project on Tuesday, with Prime Minister Abiy Ahmed calling it a "great achievement for all black people" despite years of diplomatic rancour over the dam with downstream neighbour Egypt. Credit: LUIS TATO/AFP via Getty Images
የኬኒያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ በበኩላቸው፤ “በአሁን አፍሪካ እያስመዘገበች ባለው ፈጣን ለውጥ የዓለም አቀፍ ስርዓት ውስጥ እንደ አጋር ብቻ ሳይሆን እንደ ዋና ተዋናይ መሆን አለባት። በዘላቂ ትብብር የአየር ንብረት አደጋን ማስወገድ ይችላል ያሉት ፕሬዚዳንቱ፤ በኢኮኖሚው የአፍሪካን ትክክለኛ ቦታ በማስጠበቅ ዘመናዊ፣ አረንጓዴና ሁሉን አቀፍ የኢንዱስትሪ መሰረት መገንባት ያስፈልጋል” ብለዋል።

ፕሬዚዳንቱ አክለውም፤ የአየር ንብረት ራዕይን እውን ለማድረግ በሁለት ግንቦች ላይ እርምጃ መውሰድ እንደሚያስፈልግ ጠቅሰው፤ በዚህም አፍሪካ ወጥ የሆነ ተሳትፎዋን ማጠናከር እንዳለባት ተናግረዋል።

አፍሪካ በቂ ሀብትና ወጣት የሰው ሀይል ቢኖራትም ማደግ ባለባት ልክ ባለማደጓ የዓለም አቀፍ ስርዓቱ አህጉሪቱን ወደ ኋላ የሚጎትቱትን መዋቅራዊ መሰናክሎች ማፍረስ እንዳለበት ተናግረዋል።

በዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ የተባበረች የአፍሪካን ድምፅ እያቀረብን ነው ያሉት ፕሬዚዳንቱ፤ የአየር ንብረትን ጨምሮ ስልታዊና የተቀናጁ መፍትሄዎችን ለመፍጠር እየሰራን ነው ብለዋል።

ለሶስት ቀናት በሚቀጥለው በዚህ ጉባዔ ንግግር ያደረጉትን የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶን ጨምሮ፣ የጂቡቲ ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦማር ጊሌ፣ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ኮሚሽነር መህሙድ አሊ ዩሱፍን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት መሪዎችና ተወካዮች ተገኝተዋል።

[ ደመቀ ከበደ ፡ ከአዲስ አበባ ]

Share

Published

By Demeke Kebede
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service