ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ ጳጉሜን 4/2017ዓም ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ከሌሎች ጥሪ ከተደረገላቸው የተለያዩ አገራት መሪዎች ጋር በይፋ መርቀዋል።
የአፍሪካ እና ካሪቢያን መሪዎች ተወካዮቻቸው በግድቡ ምረቃ ላይ ተገኝተው ምርቃቱን ተካፍለዋል።
በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ምረቃ ሥነ-ሥርዓት ላይ የጂቡቲው ፕሬዚዳንት ኦማር ጌሌ፣ የደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር፣ የሶማሊያው ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሐሙድ፣ የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ፣ የባርቤዶሷ ጠቅላይ ሚኒስትር ሚያ ሞትሊ፣ የስዋቲኒ ጠቅላይ ሚኒስትር ሚሶ ድላሚኒ እንዲሁም የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ማሕሙድ ዓሊ ዩሱፍ እና የተመድ ምክትል ዋና ጸሐፊ እና በተመድ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ክላቨር ጋቴቴ ተገኝተዋል።

Salva Kiir, president of South Sudan, William Ruto, Kenya's president, Abiy Ahmed, Ethiopia's prime minister, Zinash Tayachew, his wife, from left to center, and other dignitaries at the Grand Ethiopian Renaissance Dam (GERD) opening ceremony in Guba, Ethiopia, on Tuesday, Sept. 9, 2025. Ethiopia inaugurated on Tuesday Africa's biggest hydroelectric dam, a colossal feat of engineering that could power homes and industries across East Africa, while deepening a years-long dispute with Egypt and Sudan over the Nile's flow. Credit: Bloomberg/Bloomberg via Getty Images
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በታላቁ የህዳሴ ግድብ ምርቃት ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ በቅርቡ ከ30 ቢሊየን ዶላር በላይ ወጪ የሚጠይቁ ሜጋ ፕሮጀክቶችን እንደምትገነባ ገልጸዋል።
በንግግራቸውም፤
ኢትዮጵያ በመጪዎቹ ጥቂት ጊዜያት ህዳሴን የሚስተካከል ለሰላማዊ ዓላማ ብቻ የሚውል የኒውኪሊየር ተቋም ግንባታና በአፍሪካ ግዙፉ የአየር ማረፊያ ግንባታ ይጀመራል ብለዋል።
የመጀመሪያው የጋዝ ፋብሪካ ከጥቂት ሳምንታት በኋላ ይመረቃል፤ ከእሱ በ10 እጥፍ የሚበልጥ ሁለተኛው የጋዝ ፋብሪካ ግንባታ በምርቃቱ ቀን ይጀመራል።
የጋዝ ማውጣት ሂደቱ ከተጀመረ በወር ባነሰ ጊዜ ውስጥ የነዳጅ ዘይት ማጣሪያ ሥራና በቅርቡ የተፈረመው የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ ይጀመራል።
በመጪዎቹ አምስትና ስድስት ዓመታት በትንሹ 1.5 ሚሊየን ቤቶች ይገነባሉ ሲሉ ተናግረዋል።
የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ምርቃት ላይ የተገኙት የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሃሰን ሼክ መሀመድ "ኢትዮጵያ ያስመረቀችው የህዳሴ ግድብ በቀጠናው ላሉ ህዝቦች ሁሉ ታሪካዊ ቀን ነው፡፡ በቀጠናው የሚፈለገውን እድገትና ብልጽግና ለመፍጠር በጋራና በመተማመን መስራት ይገባል፡፡ለዚህም ሶማሊያ የጎረቤት ሀገራት ሰላምና እድገት ለሚያጠናክሩ ተግባራትን በትብብር ለመስራት ዝግጁ ናት" ብለዋል፡፡

Hassan Sheikh Mohamud, Somalia's president, center, at the Grand Ethiopian Renaissance Dam (GERD) opening ceremony in Guba, Ethiopia, on Tuesday, Sept. 9, 2025. Ethiopia inaugurated on Tuesday Africa's biggest hydroelectric dam, a colossal feat of engineering that could power homes and industries across East Africa, while deepening a years-long dispute with Egypt and Sudan over the Nile's flow. Credit: Bloomberg/Bloomberg via Getty Images

William Ruto, Kenya's president, during the Grand Ethiopian Renaissance Dam (GERD) opening ceremony in Guba, Ethiopia, on Tuesday, Sept. 9, 2025. Ethiopia inaugurated on Tuesday Africa's biggest hydroelectric dam, a colossal feat of engineering that could power homes and industries across East Africa, while deepening a years-long dispute with Egypt and Sudan over the Nile's flow. Credit: Bloomberg/Bloomberg via Getty Images
[ ደመቀ ከበደ ፡ ከአዲስ አበባ ]