በቻይና የገንዘብ ድጋፍ የተገነባው የአፍሪካ የበሽታ መቆጣጠሪያና መከላከያ ማዕከል (አፍሪካ ሲዲሲ) ተመረቀ

አምባሳደር ምስጋኑ አረጋ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ደኤታ ሆነው ተሾሙ

African CDC (Centers for Disease Control).jpg

The building of African CDC (Centers for Disease Control) headquarters during the inauguration ceremony in Addis Ababa, Ethiopia, on January 11, 2023. Credit: AMANUEL SILESHI/AFP via Getty Images

በአዲስ አበባ በተለምዶ ኃይሌ ጋርመንት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በሚገኘው የአፍሪካ መንደር (African Village) የተገነባው የአፍሪካ የበሽታ መቆጣጠሪያና መከላከያ ማዕከል (አፍሪካ ሲዲሲ) ዋና መሥሪያ ቤት ተመረቀ።

ማዕከሉ ከቻይና መንግስት በተበረከተ 80 ሚሊዮን ዶላር የተገነባ ሲሆን፤ የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሺን ጋንግ እና የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሙሳ ፋኪ ማሃማት በተገኙበት ጥር 3 ቀን 2015 ተመርቆ ሥራ ጀምሯል።
በምረቃ ሥነ ስርዓቱ ላይም በአፍሪካ ሕብረት የቻይና አምባሳደር ቻንግቹን፣ በኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕብረት አባል አገራት አምባሳደሮች እና በኢትዮጵያ የሚገኙ የቻይና ኩባንያዎች ተወካዮች ተገኝተዋል።

ማዕከሉ 90 ሺሕ ሜትር ስኩዌር አጠቃላይ ስፋት ላይ ያረፈ ሲሆን፤ የድንገተኛ አደጋ ኦፕሬሽን ማዕከል፣ የመረጃ ማዕከል፣ የላቦራቶሪ፣ የስልጠና ማዕከል፣ የኮንፈረንስ ማዕከል፣ ቢሮዎች እና አፓርታማዎችን እንዳሉት ተነግሯል።

ሹመት

በኳታርና የተባበሩት መንግሥታት የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር የነበሩት ምስጋኑ አረጋ ጥር 2 ቀን 2015 በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሚኒስትር ደኤታ ሆነው ተሹመዋል።
አምባሳደር ምስጋኑ ሚኒስትር ደኤታ ከመሾማቸው በፊት ከ2021አንስቶ የኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሆነ በመሥራት ላይ ነበሩ።

Share

Published

Updated

By Stringer Report
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service