ፖሊስ፤ በሲድኒ ቦንዳይ የገበያ ማዕከል የስለት ጥቃት ሳቢያ ስድስት ሰዎች ሞተዋል፣ በርካቶች 'በፅኑዕ' ቆስለዋል

ለጊዜው ማንነቱ ያልተገለጠ አንድ ግለሰብ የዘጠኝ ወር ሕፃን ልጅን ጨምሮ በርካታ ሰዎችን በስለት ወግቶ ያቆሰለ ሲሆን ስድስት ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል፤ ግለሰቡም በአንዲት የፖሊስ ሠራዊት አባል ተገድሏል።

Police.jpg

Witnesses have described people fleeing from Westfield Bondi Junction en masse. Credit: Photo by DAVID GRAY/AFP via Getty Images

ዛሬ ቅዳሜ ኤፕሪል 13 / ሚያዝያ 5 ከቀትር በኋላ ሲድኒ ቦንዳይ ጁንክሽን ዌስትፊልድ የገበያ ማዕከል ባደረሰው የጩቤ ጥቃት በርካታ ሰዎች መቁሰላቸውንና ስድስት ሰዎች ሕይወታቸውን ማጣታቸውን አስታወቀ።

የኒው ሳውዝ ዌይልስ አምቡላንስ በበኩሉ አንድ የዘጠኝ ወር ሕፃንን ጨምሮ ዘጠኝ የቆሰሉ ሰዎችን ወደ ሆስፒታል ማጓጓዙን ገልጧል።
Ambulance.jpg
Credit: Photo by DAVID GRAY/AFP via Getty Images
ከቆሰሉትም ውስጥ የተወሰኑቱ በብርቱ ወይም በፅኑዕ የቆሰሉ መሆኑ ተመልክቷል።

ፖሊስ ምርመራ እያካሔደ መሆኑንና ጥቃት ፈፃሚው ግለሰብ ብቻውን ጥቃቱን የሰነዘረ በመሆኑ ተያያዥ ስጋት የሌለ መሆኑን ገልጧል።
Shoppers.jpg
Families walk out of the Westfield Bondi Junction shopping mall after a stabbing incident in Sydney on 13 April, 2024. Credit: Getty / David Gray
አክሎም፤ የጥቃት ፈፃሚው ግለሰብ ማንነትና ጥቃቱን ለመፈፀም ምን እንዳነሳሳው ለጊዜው በውል ያልታወቀ መሆኑን አስታውቋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ በበኩላቸው በክስተቱ ጥልቅ ሐዘን የተሰማቸው መሆኑን ገልጠዋል፣ ለቤተሰቦች መፅናንትንና ጥቃቱን ለገቱት የፖሊስ መኮንንና አገልግሎት ለሰጡ ሁሉ ምስጋናቸውን አቅርበርዋል።

Share

Published

Updated

By Kassahun Seboqa Negewo, NACA
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service