ፖሊስ፤ በሲድኒ ቦንዳይ የገበያ ማዕከል የስለት ጥቃት ሳቢያ ስድስት ሰዎች ሞተዋል፣ በርካቶች 'በፅኑዕ' ቆስለዋል

ለጊዜው ማንነቱ ያልተገለጠ አንድ ግለሰብ የዘጠኝ ወር ሕፃን ልጅን ጨምሮ በርካታ ሰዎችን በስለት ወግቶ ያቆሰለ ሲሆን ስድስት ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል፤ ግለሰቡም በአንዲት የፖሊስ ሠራዊት አባል ተገድሏል።

Police.jpg

Witnesses have described people fleeing from Westfield Bondi Junction en masse. Credit: Photo by DAVID GRAY/AFP via Getty Images

ዛሬ ቅዳሜ ኤፕሪል 13 / ሚያዝያ 5 ከቀትር በኋላ ሲድኒ ቦንዳይ ጁንክሽን ዌስትፊልድ የገበያ ማዕከል ባደረሰው የጩቤ ጥቃት በርካታ ሰዎች መቁሰላቸውንና ስድስት ሰዎች ሕይወታቸውን ማጣታቸውን አስታወቀ።

የኒው ሳውዝ ዌይልስ አምቡላንስ በበኩሉ አንድ የዘጠኝ ወር ሕፃንን ጨምሮ ዘጠኝ የቆሰሉ ሰዎችን ወደ ሆስፒታል ማጓጓዙን ገልጧል።

Ambulance.jpg
Credit: Photo by DAVID GRAY/AFP via Getty Images

ከቆሰሉትም ውስጥ የተወሰኑቱ በብርቱ ወይም በፅኑዕ የቆሰሉ መሆኑ ተመልክቷል።

ፖሊስ ምርመራ እያካሔደ መሆኑንና ጥቃት ፈፃሚው ግለሰብ ብቻውን ጥቃቱን የሰነዘረ በመሆኑ ተያያዥ ስጋት የሌለ መሆኑን ገልጧል።

Shoppers.jpg
Families walk out of the Westfield Bondi Junction shopping mall after a stabbing incident in Sydney on 13 April, 2024. Credit: Getty / David Gray

አክሎም፤ የጥቃት ፈፃሚው ግለሰብ ማንነትና ጥቃቱን ለመፈፀም ምን እንዳነሳሳው ለጊዜው በውል ያልታወቀ መሆኑን አስታውቋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ በበኩላቸው በክስተቱ ጥልቅ ሐዘን የተሰማቸው መሆኑን ገልጠዋል፣ ለቤተሰቦች መፅናንትንና ጥቃቱን ለገቱት የፖሊስ መኮንንና አገልግሎት ለሰጡ ሁሉ ምስጋናቸውን አቅርበርዋል።


1 min read

Published

Updated

By Kassahun Seboqa Negewo, NACA

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now