ዛሬ ቅዳሜ ኤፕሪል 13 / ሚያዝያ 5 ከቀትር በኋላ ሲድኒ ቦንዳይ ጁንክሽን ዌስትፊልድ የገበያ ማዕከል ባደረሰው የጩቤ ጥቃት በርካታ ሰዎች መቁሰላቸውንና ስድስት ሰዎች ሕይወታቸውን ማጣታቸውን አስታወቀ።
የኒው ሳውዝ ዌይልስ አምቡላንስ በበኩሉ አንድ የዘጠኝ ወር ሕፃንን ጨምሮ ዘጠኝ የቆሰሉ ሰዎችን ወደ ሆስፒታል ማጓጓዙን ገልጧል።

ከቆሰሉትም ውስጥ የተወሰኑቱ በብርቱ ወይም በፅኑዕ የቆሰሉ መሆኑ ተመልክቷል።
ፖሊስ ምርመራ እያካሔደ መሆኑንና ጥቃት ፈፃሚው ግለሰብ ብቻውን ጥቃቱን የሰነዘረ በመሆኑ ተያያዥ ስጋት የሌለ መሆኑን ገልጧል።

አክሎም፤ የጥቃት ፈፃሚው ግለሰብ ማንነትና ጥቃቱን ለመፈፀም ምን እንዳነሳሳው ለጊዜው በውል ያልታወቀ መሆኑን አስታውቋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ በበኩላቸው በክስተቱ ጥልቅ ሐዘን የተሰማቸው መሆኑን ገልጠዋል፣ ለቤተሰቦች መፅናንትንና ጥቃቱን ለገቱት የፖሊስ መኮንንና አገልግሎት ለሰጡ ሁሉ ምስጋናቸውን አቅርበርዋል።

