ዛሬ ቅዳሜ ኤፕሪል 13 / ሚያዝያ 5 ከቀትር በኋላ ሲድኒ ቦንዳይ ጁንክሽን ዌስትፊልድ የገበያ ማዕከል ባደረሰው የጩቤ ጥቃት በርካታ ሰዎች መቁሰላቸውንና ስድስት ሰዎች ሕይወታቸውን ማጣታቸውን አስታወቀ።
የኒው ሳውዝ ዌይልስ አምቡላንስ በበኩሉ አንድ የዘጠኝ ወር ሕፃንን ጨምሮ ዘጠኝ የቆሰሉ ሰዎችን ወደ ሆስፒታል ማጓጓዙን ገልጧል።

Credit: Photo by DAVID GRAY/AFP via Getty Images
ፖሊስ ምርመራ እያካሔደ መሆኑንና ጥቃት ፈፃሚው ግለሰብ ብቻውን ጥቃቱን የሰነዘረ በመሆኑ ተያያዥ ስጋት የሌለ መሆኑን ገልጧል።

Families walk out of the Westfield Bondi Junction shopping mall after a stabbing incident in Sydney on 13 April, 2024. Credit: Getty / David Gray
ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ በበኩላቸው በክስተቱ ጥልቅ ሐዘን የተሰማቸው መሆኑን ገልጠዋል፣ ለቤተሰቦች መፅናንትንና ጥቃቱን ለገቱት የፖሊስ መኮንንና አገልግሎት ለሰጡ ሁሉ ምስጋናቸውን አቅርበርዋል።