ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ ከእሥር ተፈታ

የኢትዮጵያ ኢንሳይደር የበይነ መረብ ብዙሃን መገናኛ መሥራችና ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ ከ 5ቀናት እሥራት በኋላ ዛሬ ዓርብ ሰኔ 6 ቀን 2017 ዓ.ም ከእሥር መፈታቱ ታውቋል፡፡

Journalist Tesfalem Woldeyes.png

Credit: EI

ድርጅቱ ሀቅ ሚዲያ እና ኮሚኒኬሽን "ተስፋለም በእሥር ላይ በቆየባቸው ባለፉት ቀናት አስፈላጊውን ትብብር" ላደረጉ ሁሉ በማለት ምስጋና አቅርቧል።

የአዲስ አበባ ከተማ ሰበር ሰሚ ችሎት ትናንት ሐሙስ ሰኔ 5 ቀን 2017 ዓ.ም "የሥር ፍርድ ቤቶች የጋዜጠኛውን የዋስትና መብት መጠበቃቸውን መሠረታዊ የሕግ ጥሰት ያልተፈፀመበት እና ሕግን የተከተለ ሆኖ ስላገኘነው" ሲል የሥር ፍርድ ቤቶች የሰጡትን ውሳኔ አጽንቷል።

ይሁንና ጋዜጠኛው ትናንት ሳይፈታ እሥር ቤት አድሯል።

ተስፋለም ከእሥር እንዲለቀቅ የሙያ ማኅበራት፣ ሲቪክ ድርጅቶች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት፣ ግለሰቦችና ጉዳዩ ያገባናል ያሉ ሁሉ ሲወተውቱ ቆይተዋል።

ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ "ሐሰተኛ መረጃ ማሰራጨት" በሚል ተጠርጥሮ በፀጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ሥር የዋለው እሑድ ሰኔ 1 ቀን 2017 ዓ.ም. ነበር።

Share

Published

Updated

By Stringer Report
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service