SKIP TO MAIN CONTENT

ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ ከእሥር ተፈታ

የኢትዮጵያ ኢንሳይደር የበይነ መረብ ብዙሃን መገናኛ መሥራችና ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ ከ 5ቀናት እሥራት በኋላ ዛሬ ዓርብ ሰኔ 6 ቀን 2017 ዓ.ም ከእሥር መፈታቱ ታውቋል፡፡

Journalist Tesfalem Woldeyes.png
Credit: EI

1 min read

Published

Updated

By Stringer Report

Source: SBS


Skip to article content

ድርጅቱ ሀቅ ሚዲያ እና ኮሚኒኬሽን "ተስፋለም በእሥር ላይ በቆየባቸው ባለፉት ቀናት አስፈላጊውን ትብብር" ላደረጉ ሁሉ በማለት ምስጋና አቅርቧል።

የአዲስ አበባ ከተማ ሰበር ሰሚ ችሎት ትናንት ሐሙስ ሰኔ 5 ቀን 2017 ዓ.ም "የሥር ፍርድ ቤቶች የጋዜጠኛውን የዋስትና መብት መጠበቃቸውን መሠረታዊ የሕግ ጥሰት ያልተፈፀመበት እና ሕግን የተከተለ ሆኖ ስላገኘነው" ሲል የሥር ፍርድ ቤቶች የሰጡትን ውሳኔ አጽንቷል።

ይሁንና ጋዜጠኛው ትናንት ሳይፈታ እሥር ቤት አድሯል።

ተስፋለም ከእሥር እንዲለቀቅ የሙያ ማኅበራት፣ ሲቪክ ድርጅቶች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት፣ ግለሰቦችና ጉዳዩ ያገባናል ያሉ ሁሉ ሲወተውቱ ቆይተዋል።

ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ "ሐሰተኛ መረጃ ማሰራጨት" በሚል ተጠርጥሮ በፀጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ሥር የዋለው እሑድ ሰኔ 1 ቀን 2017 ዓ.ም. ነበር።


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Stream now