ዊሊያም ሩቶ የኬንያ 5ኛው ፕሬዚደንት ሆነው ቃለ መሐላ ፈፀሙ

በፕሬዚደንት ሩቶ በዓለ ሲመት ላይ ከተጋባዥ እንግዶች ውስጥ የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ ሌሎች ርዕሰ መንግሥታትና ርዕሰ ብሔሮች፣ እንዲሁም ዲፕሎማቶች ተገኝተዋል።

Kenyan President William Ruto .jpg

Kenya's fifth President William Ruto. Credit: Billy Mutai/Anadolu Agency via Getty Images

አዲሱ የኬንያ ተመራጭ ፕሬዚደንት ዊሊያም ሩቶ ዛሬ ሴፕቴምበር 13, 2014 / መስከረም 3, 2015 በአካባቢው ሰዓት አቆጣጠር ከቀትር በኋላ በካሳራኒ ዓለም አቀፍ ስታዲየም ተገኝተው ቃለ መሐላ በመፈፀም 5ኛው የኬንያ ፕሬዚደንት ሆነዋል።

የእሳቸውን ቃለ መሐላ ተከትለውም ምክትላቸው ሪጊታ ጋቻዎ ቃለ መሐላ ፈፅመዋል።

በፕሬዚደንት ሩቶ በዓለ ሲመት ላይ የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ የዑጋንዳ ፕሬዚደንት ዩዌሪ ሙሴቪኒ፣ የሩዋንዳው ፕሬዚደንት ፖል ካጋሜና የታንዛኒያ ፕሬዚደንት ሳሚያ ሱሉሁ፣ ሌሎች ርዕሰ ብሔሮችና ዲፕሎማቶች ተገኝተዋል።


1 min read

Published

Updated

By Kassahun Seboqa Negewo

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now