የአውስትራሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ቀለበት አሰሩ

የአውስትራሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ ዛሬ ሐሙስ ማለዳ ላይ ከፍቅረኛቸው ጆዲ ሃይደን ጋር ቀለበት ማሰራቸውን በማኅበራዊ ሚዲያ "She said yes" ሲሉ አስታውቀዋል።

ALBO AND jODIE.jpg

The prime minister announced the engagement on social media. Credit: Supplied

አቶ አልባኒዚ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ቀለበት ያሰሩ የመጀመሪያው የአውስትራሊያ መሪ ሆነዋል።

አያሌ የሌበር ፓርቲ ባለስልጣናት፣ የሥራ ባልደረቦችና ዜጎችም የ "እንኳን ደስ አላችሁ" መልዕክቶችን አስተላልፈዋል።

አልባኒዚና ሃይደን ለመጀመሪያ ጊዜ የተገናኙት በወርኅ ማርች 2020 ሜልበርን ውስጥ በተካሔደ አንድ የንግድ እራት ግብዣ ላይ ነው።

በእራት ምሽቱ ወቅት አቶ አልባኒዚ እሳቸው የሚደግፉት የደቡብ ሲድኒ የአውስትራሊያ እግር ኳስ ቡድን ራቢቶስ ደጋፊ እንዳለ ሲጠይቁ፤ ሃይደን "እኔ አለሁ" በማለት ምላሽ ሰጡ።

አጋጣሚዋ አስባብ ሆና መጠጥ እየተጎነጩ ሊያወጉ በመካከለኛው ምዕራብ ሲድኒ ኒውታውን ከሚገኘው የወጣት ሄንሪ ቢራ መጥመቂያ በቀጠሮ ተገናኙ።

ፍቅር ተጀመረ፤ ሰረፀ፤ ለሠርግ ለሚያደርሰው ቀለበት በቃ።

የ45 ዓመቷ ሃይደን ያደጉት በኒው ሳውዝ ዌይልስ ማዕከላዊ የባሕር ዳርቻ ሲሆን፤ በጡረታ አበል ኢንዱስትሪ ለረጅም ጊዜያት በሙያተኝነት ሠርተዋል።

ጋብቻ ሲፈፅሙም ለሃይደን የመጀመሪያ፤ ከቀድሞ ሚስታቸው ካርሜል ቲበት በ2019 ለተፋቱት አልባኒዚ ሁለተኛ ይሆናል።


1 min read

Published

By Kassahun Seboqa Negewo

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now