ቪክቶሪያ ላይ ተጥለው ያሉት የኮሮናቫይረስ ገደቦች ከነገ ሐሙስ እኩለ ለሊት ጀምሮ ይረግባሉ

*** ከቤት ሲወጡ የፊት ጭምብል የማጥለቅ ግዴታ አይኖርም

SBS Amharic

Source: SBS Amharic

የቪክቶሪያ ተጠባባቂ ፕሪሚየር ጄምስ ሜሊኖ ሜልበርንና ሪጂናል ቪክቶሪያ ላይ ተጥለው የነበሩት የኮሮናቫይረስ ገደቦች ከነገ ሐሙስ ጁን 17 ከምሽቱ 11.59pm ጀምሮ እንደሚረግቡ ዛሬ አስታውቀዋል። 

በዚህም መሠረት፤

ማኅበራዊ

  • ቤትዎ ውስጥ በየቀኑ ሁለት ጎብኚዎችዎን ሊያስተናግዱ ይችላሉ
  • ከቤት ውጪ በቡድን እስከ 20 ሰዎች መሰባሰብ ይፈቀድላቸዋል

የኪሎ ሜትሮች ገደብ

  • ቀደም ሲል ከመኖሪያ ቤትዎ ከ25 ኪሎ ሜትሮች ርቀው በላይ እንዳይጓዙ ተጥሎ የነበረው ገደብ ተንስቷል።
  • የሜልበርን ነዋሪዎች ወደ ሪጂናል ቪክቶሪያ መጓዝ ይችላሉ።

የፊት ጭምብሎች

  • በቤት ውስጥ የ1 ነጥብ 5 ሜትሮች ርቀትን ለመጠበቅ በማይቻልባቸው ሁኔታዎች ካልሆነ በስተቀር የፊት ጭምብል ለማጠለቅ ግዴታ አይኖርም።

የምግብና መስተንግዶ ሥፍራዎች

  • የምግብና መስተንግዶ ግልጋሎት ሰጪዎች አንድ ሰው በሁለት ስኩየር ሜትር ርቀት ማስተናገድ ይችላሉ።

 

  • አካላዊ እንቅስቃሴ ማካሄጃ፣ የቤት ውስጥ መስተንግዶ ሰጪዎች ግልጋሎቶችን መስጠት ይጀምራሉ።

 


1 min read

Published

By NACA

Presented by Kassahun Seboqa Negewo


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now