SKIP TO MAIN CONTENT

ቪክቶሪያ ላይ ተጥለው ያሉት የኮሮናቫይረስ ገደቦች ከነገ ሐሙስ እኩለ ለሊት ጀምሮ ይረግባሉ

*** ከቤት ሲወጡ የፊት ጭምብል የማጥለቅ ግዴታ አይኖርም

SBS Amharic
Source: SBS Amharic

1 min read

Published

By NACA

Presented by Kassahun Seboqa Negewo


Skip to article content

የቪክቶሪያ ተጠባባቂ ፕሪሚየር ጄምስ ሜሊኖ ሜልበርንና ሪጂናል ቪክቶሪያ ላይ ተጥለው የነበሩት የኮሮናቫይረስ ገደቦች ከነገ ሐሙስ ጁን 17 ከምሽቱ 11.59pm ጀምሮ እንደሚረግቡ ዛሬ አስታውቀዋል። 

በዚህም መሠረት፤

ማኅበራዊ

  • ቤትዎ ውስጥ በየቀኑ ሁለት ጎብኚዎችዎን ሊያስተናግዱ ይችላሉ
  • ከቤት ውጪ በቡድን እስከ 20 ሰዎች መሰባሰብ ይፈቀድላቸዋል

የኪሎ ሜትሮች ገደብ

  • ቀደም ሲል ከመኖሪያ ቤትዎ ከ25 ኪሎ ሜትሮች ርቀው በላይ እንዳይጓዙ ተጥሎ የነበረው ገደብ ተንስቷል።
  • የሜልበርን ነዋሪዎች ወደ ሪጂናል ቪክቶሪያ መጓዝ ይችላሉ።

የፊት ጭምብሎች

  • በቤት ውስጥ የ1 ነጥብ 5 ሜትሮች ርቀትን ለመጠበቅ በማይቻልባቸው ሁኔታዎች ካልሆነ በስተቀር የፊት ጭምብል ለማጠለቅ ግዴታ አይኖርም።

የምግብና መስተንግዶ ሥፍራዎች

  • የምግብና መስተንግዶ ግልጋሎት ሰጪዎች አንድ ሰው በሁለት ስኩየር ሜትር ርቀት ማስተናገድ ይችላሉ።

 

  • አካላዊ እንቅስቃሴ ማካሄጃ፣ የቤት ውስጥ መስተንግዶ ሰጪዎች ግልጋሎቶችን መስጠት ይጀምራሉ።

 


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Stream now