ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ከእስር ተለቀቀ

የፍትሕ መጽሔት ማኔጂንግ ኤዲተር ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በ30 ሺሕ ብር ዋስትና በዛሬዉ ዕለት ከእስር መፈታቱ ታውቋል።

Journalist Temesgen Desalegn.jpg

Journalist Temesgen Desalegn. Credit: PR

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የጸረ ሽብርና ህገ መንግስታዊ ችሎት ትላንት ኀዳር 6 ቀን 2015 በዋለዉ ችሎት ጋዜጠኛው በ30 ሺሕ ብር ዋስትና ከእስር እንዲፈታ ቢወስንም የቂልንጦ ማረሚያ ቤት ለመልቀቅ ፍቃደኛ ሳይሆን ማደሩ ይታወቃል።

ዛሬ ኀዳር 7 ቀን 2015 ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ለ176 ቀናት የእስር ቆይታ በኋላ መፈታቱን ቤተሰቦቹ አስታውቀዋል።


1 min read

Published

Updated

By Stringer Report

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now