እሥራኤል ከኢትዮጵያ ለፋሲካ በዓል ሥነ ሥርዓት ወደ ኢየሩሳሌም የሚጓዙ ኢትዮጵያውያን የክርስትና እምነት ተከታዮች ላይ እገዳ ጣለች

*** ከ135 ሺህ በላይ የደቡብ አውስትራሊያ መራጮች ከቅዳሜው ዋና የምርጫ ቀን በፊት ቀድመው ድምፅ ሰጡ።

News

Ethiopian Christian Orthodox worshippers walk along the Via Dolorosa during the Good Friday procession in Jerusalem's old city on April 2, 2010. Source: Getty

የእሥራኤል ኢሚግሬሽን ባለስልጣናት ከኢትዮጵያ ለፋሲካ በዓል ሥነ ሥርዓት ወደ እሥራእኤል በቡድን የሚጓዙ ኢትዮጵያውያን የክርስትና እምነት ተከታዮች እንዳይገቡ መመሪያ መስጠቱን የእሥራኤል ብዙኅን መገናኛዎች አስታወቁ።

ኢትዮጵያውያን የክርስትና እምነት ተከታዮች በየዓመቱ የሚከበረውን የትንሣእኤ በዓል በቡድን ወደ እሥራኤል ተጉዘው ከዕለተ ስቅለት ዓርብ ጀምረው ኢየሩሳሌም ውስጥ ላለፉት በርካታ ዓመታት ሲያከብሩ ቆይተዋል።  

ሆኖም የእሥራእኤል ባለስልጣናት በበዓለ ትንሣኤ ስም ወደ እሥራኤል የሚገቡ ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው ላይመለሱ ይችላሉ በሚል ስጋት በዘንድሮው የቡድን መንፈሳዊ የትንሣኤ በዓል ተጓዦች ላይ እገዳ ጥለዋል። 
 
ይህንኑ አስመልክቶም የሥነ ሕዝብና ኢሚግሬሽን ባለስልጣን ኢትዮጵያ ውስጥ ካለው የእርስ በእርስ ጦርነቱ ጋር ተያይዞ "ቱሪስቶቹ ላይመለሱ" እንደሚችሉ የሚያሳስብ ደብዳቤ ለእሥራኤል ቱሪዝም ኤጄንሲዎች መላኩን የሚዲያ አውታሮቹ ዘግበዋል። 
 
ደብዳቤው እሥራኤልን ለመጎብኘት የሚሹ ኢትዮጵያውያን በግለሰብ ደረጃ የኢሚግሬሽን ባለስልጣንን በኦንላይን ማግኘት እንደሚችሉ ማስፈሩም ተገልጧል። 
 
ዘገባዎቹን አስመልክቶ የኢሚግሬሽን ባለስልጣን በሰጠው ምላሽ "ላለፉት ዓመታት ወደ እሥራኤል በቡድን ከኢትዮጵያ የመጡ ቱሪስቶች ወደ አገራቸው አልተመለሱም፤ ሕጋዊ ባልሆነ መንገድ [እሥራእኤል ውስጥ] ቀርተዋል" ብሏል። 
 
ይህ በእንዲህ እንዳለም፤ እሥራኤል 3,000 ቤተ እሥራኤላውያንን ከኢትዮጵያ ለመውሰድ ከውሳኔ ላይ መድረሷ ተነግሯል። 
 
እሥራኤል ቤተ እሥራኤላውያኑን ለመውሰድ ዘለግ ላለ ጊዜ ስታንገራግር እንደንበረና ከይሁንታ ውሳኔ ላይ ለመድረስ ግድ የተሰኘችው ሩስያውያንና ቱክሬናውያን ስደተኞችን ለመቀበል ከመፍቀዷ ጋር ተያይዞ ከደረሰባት ብርቱ የአድሎኝነት ትችት ጫና ሳቢያ እንደሆነም ተመልክቷል።
 
እሥራኤል በይፋ የምትቀበላቸውን የሩስያውያንና ዩክሬናውያንን ስደተኞች ቁጥር ይፋ ባታደርግም ከ30,000 እስከ  50,000 ሳይደርሱ እንደማይቀሩ የጠቅላይ ሚኒስትር ናፍታሊ ቤኔት ቢሮ ምንጮች መጠቆማቸው ተዘግቧል።  

ምርጫ ደቡብ አውስትራሊያ

ቅዳሜ ከሚካሔደው የደቡብ አውስትራሊያ የክፍለ አገር ምርጫ በፊት የፖስታ ድምፅ መስጫ ጠያቂዎችና የአካል ቅድመ ዕለተ ምርጫ ድምፅ ሰጪዎች ቁጥር በእጥፍ ጨመረ።   

የደቡብ አውስትራሊያ የምርጫ ኮሚሽን እንዳስታወቀው ከ 135 ሺህ በላይ [[135,417]] መራጮች ከቅዳሜው ዋና የምርጫ ቀን በፊት ቀድመው ድምፃቸውን ሰጥተዋል። በቅድመ ምርጫ በአብዛኛው ተሳታፊ ሆነው የተገኙት በገጠር አካባቢ ያሉ ነዋሪዎች ናቸው። 

በፖስታ የምርጫ ድምፃቸውን ለመስጠት 162,467 መራጮች አመልክተዋል።

እንዲሁም፤ ተጨማሪ 4300 በኮቪድ-19 የተጠቁ ወይም የቅርብ ንኪኪ ኖሯቸው ራሳቸውን አግልለው ያሉ የድምፅ መስጫ ወረቀቶች ካሉበት ሥፍራ ወጥተው ለመወሰድ ጠይቀዋል። 

የምርጫ ኮሚሽን ማይክ ሼሪ እንገለጡት ወሸባ ገብተው ያሉ መራጮች የድምፅ መስጫዎችን በአቅራቢያቸው ካሉ የኮቪድ ምርመራ መስጫ ወይም የፈጣን አንቲጄን መመርመሪያ ማደያ ሥፍራዎች ሔደው መውሰድ ይችላሉ።  

 


Share

Published

Updated

By NACA
Presented by Kassahun Seboqa Negewo

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
እሥራኤል ከኢትዮጵያ ለፋሲካ በዓል ሥነ ሥርዓት ወደ ኢየሩሳሌም የሚጓዙ ኢትዮጵያውያን የክርስትና እምነት ተከታዮች ላይ እገዳ ጣለች | SBS Amharic