ባለፉት 24 ሰዓታት ቪክቶሪያ ውስጥ አንድ ግለሰብ ብቻ በኮሮናቫይረስ ተይዟል - ያለፈ ሕይወት የለም

*** ቪክቶሪያ ላይ የተጣሉት የኮቨድ - 19 ገደቦች መላላት ነገ እሑድ ይፋ ይሆናል

Amharic News 17 October 2020

Joggers Yarra River Source: AAP

ባለፉት 24 ሰዓታት ቪክቶሪያ በኮሮናቫይረስ የተጠቃ አንድ ሰው ብቻ ስታመዘግብ አንዳችም ሕይወት አላለፈም።

የሜልበርን የ14 ቀናት አማካይ የቫይረሱ ተዛማችነት ቁጥር ወደ 8.1 ሲወርድ የሪጂናል ቪክቶሪያ 0.5 ደርሷል።

ምንጫቸው ያልተለየ የቫይረስ ተዛማች ቁጥሮች ወደ 17 ከፍ ብለዋል። 

የቪክቶሪያ ዋና የጤና ኃላፊ የዛሬ ቅዳሜ የቫይረሱ ተዛማች ቁጥር ወደ አንድ ማሽቆልቆል በጣሙን ደስ ያሰኛቸው መሆኑን ገልጠዋል።

በሰሜናዊ ቪክቶሪያ ሺፐርተን ባለፈው ሳምንት የሶስት ግለሰቦችን በቫይረሱ መያዝ ተከትሎ በሺህዎች የሚቆጠሩ ለኮቨድ - 19 ምርመራና በመቶዎች የሚቆጠሩትን ለወሸባ ቢዳርግም ባለፉት 24 ሰዓታት አንዳችም በቫይረሱ የተጠቃ ግለሰብ አልተመዘገበም።

የቫይረሱን ማሽቆልቆል ተከትሎ አያሌ ሜልበርናውያን ነገ ይፋ በሚሆነው የገደቦች መርገብ ላይ ለቀቅ ያለ መላላቶች እንዲደረጉ ቢሹም የፕሪሚየር አንድሩስ መንግሥት ምን ያህል ገደቦችን እንደሚያላላ ግልጽ አይደለም።

ከሰኞ ኦክቶበር 19 የኮቨድ - 19 ገደቦች መርገብ በኋላ በኦክቶበር 26 የቫይረሱን የመስፋፋት መጠን ውጤት ተመርኩዞ የደረጃ ሶስት ገደቦችን በተጨማሪ የማላላት እርምጃዎች ይወሰዳሉ። 

 

 


Share

Published

By NACA
Presented by Kassahun Seboqa Negewo

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service