ባለፉት 24 ሰዓታት ቪክቶሪያ ውስጥ አንድ ግለሰብ ብቻ በኮሮናቫይረስ ተይዟል - ያለፈ ሕይወት የለም

*** ቪክቶሪያ ላይ የተጣሉት የኮቨድ - 19 ገደቦች መላላት ነገ እሑድ ይፋ ይሆናል

Amharic News 17 October 2020

Joggers Yarra River Source: AAP

ባለፉት 24 ሰዓታት ቪክቶሪያ በኮሮናቫይረስ የተጠቃ አንድ ሰው ብቻ ስታመዘግብ አንዳችም ሕይወት አላለፈም።

የሜልበርን የ14 ቀናት አማካይ የቫይረሱ ተዛማችነት ቁጥር ወደ 8.1 ሲወርድ የሪጂናል ቪክቶሪያ 0.5 ደርሷል።

ምንጫቸው ያልተለየ የቫይረስ ተዛማች ቁጥሮች ወደ 17 ከፍ ብለዋል። 

የቪክቶሪያ ዋና የጤና ኃላፊ የዛሬ ቅዳሜ የቫይረሱ ተዛማች ቁጥር ወደ አንድ ማሽቆልቆል በጣሙን ደስ ያሰኛቸው መሆኑን ገልጠዋል።

በሰሜናዊ ቪክቶሪያ ሺፐርተን ባለፈው ሳምንት የሶስት ግለሰቦችን በቫይረሱ መያዝ ተከትሎ በሺህዎች የሚቆጠሩ ለኮቨድ - 19 ምርመራና በመቶዎች የሚቆጠሩትን ለወሸባ ቢዳርግም ባለፉት 24 ሰዓታት አንዳችም በቫይረሱ የተጠቃ ግለሰብ አልተመዘገበም።

የቫይረሱን ማሽቆልቆል ተከትሎ አያሌ ሜልበርናውያን ነገ ይፋ በሚሆነው የገደቦች መርገብ ላይ ለቀቅ ያለ መላላቶች እንዲደረጉ ቢሹም የፕሪሚየር አንድሩስ መንግሥት ምን ያህል ገደቦችን እንደሚያላላ ግልጽ አይደለም።

ከሰኞ ኦክቶበር 19 የኮቨድ - 19 ገደቦች መርገብ በኋላ በኦክቶበር 26 የቫይረሱን የመስፋፋት መጠን ውጤት ተመርኩዞ የደረጃ ሶስት ገደቦችን በተጨማሪ የማላላት እርምጃዎች ይወሰዳሉ። 

 

 


1 min read

Published

By NACA

Presented by Kassahun Seboqa Negewo


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now