ቻይናና ሰለሞን ደሴቶች ዛሬ የፀጥታ ትብብር ውል ስምምነት ላይ መድረሳቸውን አሳወቁ።
ውሉ ደቡብ ፓስፊክ ላይ ለቻይና ባሕር ኃይል ጦር ሠፈር ምሥረታ በር ሊከፍት ይችል ይሆናል የሚል ስጋትን በአውስትራሊያ፣ ኒውዝላንድና ዩናይትድ ስቴትስ ዘንድ አሳድሯል።
በሁለቱ አገራት ዘንድ የፀጥታ ውል ስምምነት ላይ መደረሱን ቤጂንግ ላይ ይፋ ያደረጉት የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ዋንግ ዌንቢን ናቸው።
አቶ ዌንቢም የትብብር ውል ስምምነቱ ቤጂንግ ከሆኒያራ ጋር ማኅበራዊ ሥርዓትን በማስፈን፣ የሰዎች ደኅነነት ጥበቃ፣ እርዳታ፣ የተፈጥሮ አደጋዎችን መከላከል እና የብሔራዊ ፀጥታ ጥበቃ ላይ ያተኮረ መሆኑን ገልጠዋል።
የሰለሞን ደሴቶች የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጀርሚያህ ማኔሌ የትብብር ውል ስምምነቱ በፊርማ መጽደቁን ለABC በአጭር የስልክ ፅሁፍ መልዕክት አረጋግጠዋል።
በመልዕክታቸውም ጠቅላይ ሚኒስትር ማናሴህ ሶጋቫሬ ስምምነቱን አስመልክተው በመጪዎቹ ቀናት ይፋ መግለጫ እንደሚሰጡበት ገልጠዋል።
የሌበር ፓርቲ የውጭ ጉዳይ ቃል አቀባይ ሴናተር ፔኒ ዎንግ የፓስፊክ ቀጣና በጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን አመራር ቸል መባሉንና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትራችውን እንኳ ወደ ደሴቲቱ መዲና ለመላክ አለመከጀላቸውን አጣቅሰው ብርቱ ትችት ሰንዝረዋል።

ከስምምነቱ የፊርማ ፀደቃ ጥቂት ቀናት ቀደም ብሎ የአውስትራሊያ የዓለም አቀፍ ልማትና የፓስፊክ ሚኒስትር ዜድ ሰሰልጃ ወደ ሆኒያራ አምርተው ከጠቅላይ ሚኒስትር ማናሴህ ሶጋቫሬ ጋር በመገናኘት የአውስራሊያን አቋም አስረድተዋል።
የቻይና የውጭ ጉዳይ ቃል አቀባይ ትብብሩ ግልፅነት የተመላው እንደሚሆንና ሌላ ሶስተኛ አገርን ዒላማ እንደማያደርግ ተናግረዋል።

