ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የቀድሞው የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጅ ዑመር ኢድሪስ ባጋጠማቸው ሕመም በሕክምና ሲረዱ ቆይተው በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የፕሬዝደንቱ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ አስታውቀዋል፡፡

Haji Idris.png

Former President of the Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council, Grand Mufti Haji Umer Idris. Credit: PD

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በቀድሞ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝደንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ሕልፈት የተሰማውን ሐዘን ገልጿል፡፡

ምክር ቤቱ ባወጣው የሐዘን መግለጫ "የሀገራችን ዋርካ እና የሁሉም አባት የነበሩት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ባጋጠማቸው ሕመም በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ወደ አኼራ ሔደዋል" ብሏል::

"ሕልፈታቸው የመላው ሀገራችን ሕዝብ ሐዘን ነው" ሲልም ምክር ቤቱ አክሎ ገልጿል፡፡

ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ላበርክቷቸው ሀገራዊና ሃይማኖታዊ አስተዋፆ በሚመጥን መልኩ ሥርዓተ ቀብራቸው በመንግሥት ደረጃ እስላማዊ ሥነ ሥርዓቱን በጠበቀ መልኩ ጠቅላይ ምክር ቤቱ ኃላፊነቱን በመውሰድ እንደሚፈፀምም አስታውቋል፡፡

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በበኩላቸው "የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ፕሬዚዳንት የነበሩት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ በማረፋቸው ሐዘን ተሰምቶኛል ። ሐጂ ዑመር በአመራር ዘመናቸው የተለያዩ ወገኖች ወደ አንድነት እንዲመጡ እና የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በሕግ ዕውቅና እንዲኖረው ያደረጉትን አስተዋጽዖ ሁሌም እናስታውሰዋለን" ብለዋል።

Share

Published

By Stringer Report
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service