Watch FIFA World Cup 2026™

LIVE, FREE and EXCLUSIVE

ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የቀድሞው የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጅ ዑመር ኢድሪስ ባጋጠማቸው ሕመም በሕክምና ሲረዱ ቆይተው በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የፕሬዝደንቱ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ አስታውቀዋል፡፡

Haji Idris.png
Former President of the Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council, Grand Mufti Haji Umer Idris. Credit: PD

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በቀድሞ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝደንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ሕልፈት የተሰማውን ሐዘን ገልጿል፡፡

ምክር ቤቱ ባወጣው የሐዘን መግለጫ "የሀገራችን ዋርካ እና የሁሉም አባት የነበሩት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ባጋጠማቸው ሕመም በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ወደ አኼራ ሔደዋል" ብሏል::

"ሕልፈታቸው የመላው ሀገራችን ሕዝብ ሐዘን ነው" ሲልም ምክር ቤቱ አክሎ ገልጿል፡፡

ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ላበርክቷቸው ሀገራዊና ሃይማኖታዊ አስተዋፆ በሚመጥን መልኩ ሥርዓተ ቀብራቸው በመንግሥት ደረጃ እስላማዊ ሥነ ሥርዓቱን በጠበቀ መልኩ ጠቅላይ ምክር ቤቱ ኃላፊነቱን በመውሰድ እንደሚፈፀምም አስታውቋል፡፡

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በበኩላቸው "የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ፕሬዚዳንት የነበሩት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ በማረፋቸው ሐዘን ተሰምቶኛል ። ሐጂ ዑመር በአመራር ዘመናቸው የተለያዩ ወገኖች ወደ አንድነት እንዲመጡ እና የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በሕግ ዕውቅና እንዲኖረው ያደረጉትን አስተዋጽዖ ሁሌም እናስታውሰዋለን" ብለዋል።


1 min read

Published

By Stringer Report

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Stream now