የቪክቶሪያ ተቃዋሚ ቡድን የSBS የይዘት ግብዓት ማዕከል ከሲድኒ ወደ ሜልበርን እንዲዛወር አሳሰበ

የቪክቶሪያ ተቃዋሚ ቡድን እስከ አንድ ሚሊየን ዶላር ድረስ የሚያወጣ የመጀመሪያ ቤት ገዢ ለሆኑ የቪክቶሪያ ነዋሪዎች 55 ሺህ ዶላር ያህል የሚቆጥብላቸው የመሬት ግብር ፖሊሲ ያለው መሆኑን አስታወቀ

op leader.jpg

Brad Pattin MP, Victorian Opposition Leader. Credit: SBS Amharic

የቪክቶሪያ ተቃዋሚ ቡድን መሪ ብራድ ባቲን በቪክቶሪያ ፓርላማ የሊብራል ፓርቲ መሰብሰቢያ አዳራሽ በጠሩት ጋዜጣዊ መግለጫ የፓርቲያቸውን የቤት፣ የንግድ፣ ጋዝና ትምህርት ፖሊሲ አብራርተዋል።

አቶ ባቲን በጋዜጣዊ መግለጫቸው የፓርቲያቸውን ፖሊሲዎች ሲያስረዱ፤ ለመጀመሪያ ጊዜ እስከ አንድ ሚሊየን የሚያወጣ ቤት ለሚገዙ የቪክቶሪያ ነዋሪዎች የመሬት ግብር እፎይታ በመስጠት 55 ሺህ ዶላር ያህል እንዲቆጥቡ የሚያስችላቸው መሆኑን ገልጠዋል።

በቂና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ለቪክቶሪያ ነዋሪዎች ለማዳረስ የጋዝ ፍለጋና አቅርቦት እንዲካሔድ፣ እንዲሁም በግልና የሃይማኖት ትምህርት ቤቶች ክፍያ ለከፍተኛ ጫና ለተጋለጡ ወላጆች ወጪያቸው እንዲቃለል ለማድረግ ውጥን ያለው መሆኑን ተናግረዋል።
የተቃዋሚ ቡድኑ የመድብለባሕል ጉዳዮች ቃል አቀባይ ኢቫን ማልሆላንድ በበኩላቸው ቀደም ሲል በቪክቶሪያ የላይኛው ምክር ቤት ምዕራብ ሲድኒ ባቀረቡት የመከራከሪያ ሃሳብ ፤ የፌዴራል መንግሥቱ ሲድኒ ላይ ሁለተኛ የSBS ስርጭት ማዕከል ለማቆም ውሳኔ ማሳለፉና ሙጥኝ ማለቱ ከፖለቲካ ትርፍ አኳያ እንደሁ አመላክተዋል።

አቶ ማልሆላንድ አያይዘውም፤ "ቪክቶሪያ የአውስትራሊያ መድብለባሕል መዲና ናት፤ SBS ያን ሊያንፀባርቅ ይገባል"

"ቪክቶሪያ ከኒው ሳውዝ ዌይልስ የላቀ የባሕር ማዶ ተወላጆች አሏት"

እናም " ሁሉንም አውስትራሊያውያን ሊወክል ይገባል፤ አለያ የሲድኒ ስርጭት አገልግሎት ብቻ ሆኖ የቀራል" ብለዋል።

ስለሆነም "ወደ ሜልበርን ሊዛወር ይገባል" ሲሉ የሊብራል ናሽናልስ - አቋም አንፀባርቀዋል።

Share

Published

Updated

By Kassahun Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service