SKIP TO MAIN CONTENT

አቶ ጌታቸው ረዳ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ሆነው ተሾሙ

ርዕሰ መስተዳድሩ "በክልሉ የሚንቀሳቀሱ የተለያዩ የፖለቲካ ኃይሎችን ውክልና የሚያረጋግጥና አካታች የሆነ አስተዳደር በማዋቀር የክልሉን አስፈፃሚ አካል የመምራትና የማስተባበር ኃላፊነት" የተጣለባቸው መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።

G Reda.jpg
Getachew Reda, head of the interim Tigray regional administration. Credit: PHILL MAGAKOE/AFP via Getty Images

1 min read

Published

By Kassahun Seboqa Negewo

Source: SBS


Skip to article content

የሕወሓትን ከአሸባሪ ድርጅነትነት ፍረጃ ባሕር መዝገብ መፋቅን ተከትሎ የቀድሞው የክልሉ ፕሬዚደንት ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል አማካሪና የድርጅቱ ቃል አቀባይ የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ርዕሰ መስተዳድር ሆነው ተሾመዋል።

አቶ ጌታቸው የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ሆነው መሾማቸው የተገለጠው የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽሕፈት ቤት መጋቢት 14 ቀን 2015 "የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ስለማቋቋም" በሚል ባወጣው ይፋ መግለጫ ነው።

ጽሕፈት ቤቱ የኢፌዴሪ ምክር ቤት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር እንዲቋቋም ባሳለፈው ውሳኔ መሠረትና በፕሪቶሪያ ደቡብ አፍሪካ የተካሔደውን የሰላም ስምምነት ተመርኩዞ የሚኒስትሮች ምክር ቤት መጋቢት 9 ቀን 2015 "የትግራይ ክልል አካታች ጊዜያዊ አስተዳደር ደንብ" ማፅደቁንም አውስቷል።

አክሎም "ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ የሚንቀሳቀሱ የተለያዩ የፖለቲካ ኃይሎችን ውክልና የሚያረጋግጥና አካታች የሆነ አስተዳደር በማዋቀር የክልሉን አስፈፃሚ አካል የመምራትና የማስተባበር ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል" ብሏል።


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Stream now