የድርድሩ ነገር በደቡብ አፍሪካ

ከሕወሓት ተደራዳሪዎች መካከል ጄነራል ፃድቃን ገብረተንሳይ እና አቶ ጌታቸው ረዳ እንደሚገኙበት የታወቀ ሲሆን፤ በኢትዮጵያ መንግሥት በኩል በይፋ ባይገለፅም አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን፣ ዶ/ር ጌዲዮን ጤሞቴዎስና ዶ/ር ጌታቸው ጀምበር ወደ ደቡብ አፍሪካ ማቅናታቸውን ምንጮች ጠቆሙ።

Getachew Reda.jpg

Getachew Reda, Spokesperson of TPLF (R), Ambassador Redwan Hussien, National Security Advisor to Prime Minister Abiy Ahmed (L), and Attorney General Gedion Timothewos (R). Credit: Minasse Wondimu Hailu/Anadolu Agency/Getty Images / Minasse Wondimu Hailu/Anadolu Agency via Getty Images / Michael Tewelde/Xinhua via Getty Images

በኢትዮጵያ መንግሥትና በሕወሓት መካከል ዛሬ ይጀመራል ለተባለው የሰላም ንግግር የሁለቱም ወገኖች ተደራዳሪዎች ደቡብ አፍሪካ መግባታቸው እየተሰማ ነው።

ምንም እንኳ ድርድሩ የሚካሄድበት ትክክለኛ ቦታና ሰዓት በጥብቅ ምሥጢር የተያዘና እስካሁንም ያልተገለፀ ቢሆንም የሕወሓት የውጭ ጉዳዮች ቢሮ ቃል አቀባይ ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረህይወት በፃፉት የትዊተር መረጃ ተደራዳሪዎቻቸው ደቡብ አፍሪካ መግባታቸውን አስታውቀዋል።

“በአፍሪካ ኅብረት በሚመራው የኢትዮጵያ ትግራይ የሠላም ንግግር ላይ ለመገኘት ልዑካን ቡድናችን ደቡብ አፍሪካ ገብቷል” ብለዋል።
ቃል አቀባዩ አክለውም “ውጊያው ፈጥኖ እንዲቆም፣ ያልተገደበ የሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦትና የኤርትራ ኃይሎች መውጣት” ላይ ቅድሚያ አጀንዳቸው መሆኑን ገልፀዋል።

ከህወሓት ተደራዳሪዎች መካከል ጄነራል ፃድቃን ገብረተንሳይ እና አቶ ጌታቸው ረዳ እንደሚገኙበት የታወቀ ሲሆን በኢትዮጵያ መንግስት በኩል በይፋ ባይገለፅም አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን፣ ዶ/ር ጌዲዮን ጤሞቴዎስና ዶ/ር ጌታቸው ጀምበር ወደ ደቡብ አፍሪካ ማቅናታቸውን ምንጮች ጠቆሙ።

[ደመቀ ከበደ ፡ አዲስ አበባ]

Share

Published

Updated

By Demeke Kebede
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
የድርድሩ ነገር በደቡብ አፍሪካ | SBS Amharic