የአንዛክ ቀን መታሰቢያ ሥነ ሥርዓት በመላው አውስትራሊያ ተካሔደ

*** "እስከ መጨረሻው ሕቅታ ዋጋ ለመከፈል ቆርጠን ነው የተነሳነው" - የኢትዮጵያ ብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት

ANZAC DAY

Wanajeshi wasimama wima, kwenye ibada ya alafajiri ya Anzac Day, mjini Canberra ACT. Source: AAP

አውስትራሊያውያን በመላ አገሪቱ 106ኛውን የአውስትራሊያና ኒውዝላንድ ሠራዊት ኮሮች ጋሊፖሊን የረገጡበትን ቀን ከ2019 ወዲህ ዛሬ እሑድ ኤፕሪል 25 በአደባባይ ታድመው ዘከሩ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን ዛሬ ንጋት ላይ በካንብራ የአውስትራሊያ የጦርነት መታሰቢያ ተገኝተው የዝክረ መታሰቢያ ንግግር አድርገዋል።

አቶ ሞሪሰን በንግግራቸው ዕለቱን ከአውስትራሊያ ብሔራዊ ታሪክ ምዕራፍነት ጋር አያይዘው ገልጠዋል። 

አክለውም፤

"አገሪቱን አፍጋኒስታን ውስጥ ያገለገሉ ሴቶችና ወንዶች ልጆች፣ ባለቤቶች፣ ፍቅረኞች፣ ወላጆችና ዘመድ አዝማዶች፤ እንዲሁም አገር ውስጥና ባሕር ማዶ ያገለገሉ ቤተሰቦችን ሁሉ በክብር እናስባለን። የእነሱ ፍቅር፣ አበረታችነትና ፀሎቶች ወታደሮቻችን፣ ባሕረኞቻችን፣ የአየር ኃይሎቻችን፣ ነርሶቻችንና ሰላም አስከባሪዎቻችን ጸንተው እንዲቆዩ አግዟል" ብለዋል።  

 የብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት 

 የብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት ሚያዝያ 16 - 2013  ወቅታዊ አገራዊና ቀጠናዊ፣ የደህንነትና ፀጥታ ጉዳዮች አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ ኢትዮጵያውያን የኢትዮጵያን ሰላምና ደኅንነት እንዲያስጠብቁ፤ ወደማይቀለበስ ከፍታ ለማድረስም እንዲነሱ ጥሪ አድርጓል።

ምክር ቤቱ በመግለጫው ላይ "ከሦስት ዓመታት በፊት ወደ ለውጥ ጎዳና የገባነው በመንገዱ ላይ ችግሮች አይገጥሙንም በሚል እሳቤ አልነበረም፡፡ ሀገራችን ትከሻ ላይ የተቆለለውን የበዛ ችግር ከነውስብስብነቱ ተረድተን እንጂ፤ አቅልለን አይተን አልተነሳንም... ይሄንን በሚገባ አውቀን እስከ መጨረሻው ሕቅታ ዋጋ ለመከፈል ቆርጠን ነው የተነሳነው" ሲልም ለችግሮች ግንዛቤ፤ ለመፍትሔው ዕሳቤ ያለው መሆኑን አመላክቷል።
PMOE
Source: PMOE
አያይዞም፤ ኢትዮጵያውያን ሶስት ወሳኝ ዓላማዎችን በጽናት ማሳካት እንዳለባቸው ሲያሳስብ፤

  • በመጀመሪያ አንድ ወር ያህል ጊዜ የቀረውን ምርጫ ውጤታማ እናድርገው
  • ሁለተኛ ከምርጫው ጎን ለጎን ግድባችንን ባቀድነው መንገድና ጊዜ መገንባትና ሁለተኛውን ዙር የውኃ ሙሌት ማከናወን አለብን
  • እንዲሁም ኢትዮጵያን ከውስጥና ከውጭ ጠላቶቿ ታድገን ወደሚገባት ደረጃ ለመውሰድ እንድንቸል፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ በንቃትና በብስለት ከመንግሥት ጎን እንዲቆም ጥሪ እናደርጋለን
ብሏል።

 

 

 

 

 

 


Share

Published

Updated

By NACA
Presented by Kassahun Seboqa Negewo

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service