የኢትዮጵያ ልጆች ሱፐር አፕ ተመረቀ

የኢትዮጵያ ልጆች ሚዲያ በኢትዮጵያ የሙሉ ጊዜ የልጆች የቴሌቪዥን ቻናል በመጀመር ፈርቀዳጅ የሆነና በተለይም በልጆችና ቤተሰቦቻቸው ዘንድ ሠፊ ተቀባይነት በማግኘት በአወንታዊ የትውልድ ግንባታ ላይ እየሠራ የሚገኝ ተቋም ነው መተግበሪያውን ይፋ ያደረገው።

Super App.png

Credit: YeEthiopia

ተቋሙ ዓላማና ተደራሽነቱን ይበልጥ ለማስፋት በማሰብ መተግበሪያውን ማበልጸጉን ይፋ አድርጓል።

በባለፉት አሠርት ዓመታት በልጆች ዙርያ የተለያዩ ሥራዎች ሲሠራ የቆየው ተቋሙ በባለፉት ሰባት ዓመታት ደግሞ በኢትዮጵያ ልጆች ቴሌቪዥን የልጆች ፕሮግራሞችን በማቅረብ ላይ ይገኛል።

የኢትዮጵያ ልጆች ቴሌቪዥን ያስመረቀው ይህ መተግበሪያ በውስጡ 10 የሚሆኑ ይዘቶችን ማካተቱ ተገልጧል።

መተግበሪያው ያበለጸገው መሁቡብ ቴክኖሎጂስ መተግበሪያው ለልጆች አመቺ የሆነና አጠቃቀም ተብሎ ቀለል ተደርጎ የተዘጋጀ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ልጆች ቴሌቪዥን ሥራ አስኪያጅ ሕብስት አሰፋ እንደተናገሩት በተመደቡበት የሥራ ዘርፍ ተሰልፈው ከመጋረጃ ጀርባ ያሉ የተቋሙ ሰራተኞች እና ባለሙያዎች ምስጋና ይግባና ዛሬ ለዚህ በቅተናል ብለዋል።

"ተቋማችን እዚህ የመድረሱ ምስጢር የልጆቻችን ወላጆች ናቸው" ያሉት ሥራ አስኪያጇ "ስላደረጋችሁት ሁሉ ነገር እናመሰግናለን" ብለዋል።


1 min read

Published

Updated

By Stringer Report

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now