የአውስትራሊያ ነዋሪ ኢትዮጵያውያን ለተፈናቃይ ወገኖች መርጃ የሚውል 178 ሺህ ዶላርስ ቸሩ

*** "በጦርነት ተፈናቅለው ጧሪያቸውን ያጡ፣ ገቢያቸውንና ሥራቸውን ያጡ ብዙ ናቸው። ይኼ ማኅበራዊ ቀውስ ከጦርነቱ በላይ አገር ሊጎዳ የሚችል ነው" ዶ/ር መሐመድ እንድሪስ

Community

Aynalem Tesfaye. Source: SBS Amharic

በአውስትራሊያ ነዋሪ ኢትዮጵያውያን በጦርነት ሳቢያ ለተፈናቀሉ ኢትዮጵያውያን መርጃ የሚውል በዛሬው ዕለት ባካሔዱት የዙም ስብሰባ $178,000 አሰባስበዋል።

የዕለቱን ስብሰባ ያዘጋጀው "ኢትዮጵያን እናድን" አስተባባሪ አቶ አያሌው ሁንዴሳ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር  "ከሰባት ሚሊየን በላይ ኢትዮጵያውያን ተፈናቅለው በሚገኙበት ወቅት እኛ ልጆቿ የድርሻችንን ልንቸር ይገባናል" ብለዋል።
Community
Ayalew Hundessa. Source: SBS Amharic
በዕለቱ ተጋባዥ ከነበሩ ሶስት እንግዶች ውስጥ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ኤጀንሲ ምክትል ኃላፊ ዶ/ር መሐመድ እንድሪስ "በውጭ የምትገኙ ኢትዮጵያውያን የሚጠበቅባችሁን ለማድረግ ወደ ኋላ እንደማትሉ እርግጠኛ ነኝ። በ2013 - 14 የዳያስፖራው ማኅበረሰብ እንደ ዲፕሎማት አገሩን ያገለገለበት፣ በኢኮኖሚው ዘርፍ አገሩን ያገዘበትና በፖለቲካ ጫናውም እገዛ ያደረገበት ዓመት ነው።
Community
Dr Mohammed Edris. Source: SBS Amharic
"በጦርነት ተፈናቅለው ጧሪያቸውን ያጡ፣ ገቢያቸውንና ሥራቸውን ያጡ ብዙ ናቸው። ይኼ ማኅበራዊ ቀውስ ከጦርነቱ በላይ አገር ሊጎዳ የሚችል ነው። ርቀት በአገር ጉዳይ ላይ ቁልፍ ሚና ከመጫወት እንደማይገድብ ማረጋገጫ ነው። የፈረሱ ትምህርት ቤቶች፣ የጤና ተቋማት መልሰው መቋቋም አለባቸው። በጋራ ገንብተው፣ በጋራ ገንብተን፣ በጋራ የምንኮራባት አገር እንድትኖረን የእናንተን ርብርብ እጠይቃለሁ" ሲሉ ተናግረዋል።

ከእሳቸው ቀደም ብለው ተጋባዥ ተናጋሪ የነበሩት አቶ ነዓምን ዘለቀ "ከውጭ ያላችሁና በዚህ የታደማችሁ ኢትዮጵያ ከእናንተ የምትጠብቀው አለ። በርካታ ተፈናቃዮች አሉ። ከዲያስፖራው ማኅበረሰብ የሚገኘው ገቢ በጣም ወሳኝና ጠቃሚ ነው። የታደማችሁበት ዝግጅት እንዲሳካ እመኛለሁ። የምትችሉትን ሁሉ አድርጉ" ብለዋል።

ሶስተኛው ተጋባዥ ተናጋሪ የነበሩት ብርጋዲየር ጄኔራል ካሣዬ ጨመዳ በበኩላቸው "ኢትዮጵያ ልጆች አሏት። እናንተ አላችሁ። ተመልሳችሁ የምትገቡባት አገራችሁ ናት። ለኢትዮጵያ በችግሯ ቀን ይህን አድርጌላታለሁ ብላችሁ የኅሊና እርካታ የምታገኙባእት ነው" በማለት ተናግረዋል።  

   


Share

Published

By Kassahun Seboqa Negewo

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service