ኢትዮ ቴሌኮም "ቴሌ ክላውድ" ዲጂታል አገልግሎት አስጀመረ

የተለያዩ የዲጂታል አገልግሎቶችን በማስፋፋት ላይ የሚገኘው ኢትዮ ቴሌኮም የቴሌ ክላውድ ዲጂታል አገልግሎት መጀመሩን ዛሬ በሳይንስ ሙዚየም ባካሄደው መርሃ ግብር ይፋ አደርጓል።

Frehiwot Tamiru, CEO of Ethio-Telecom.jpg

Frehiwot Tamiru, CEO of Ethio-Telecom. Credit: EthioTelecom

የኢትዮ ቴሌኮም ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ በይፋዊ የማስጀመሪያ ስነ ስርዓቱ ላይእንደገለፁት፤

“የቴሌ ክላውድ አገልግሎት ተቋማት የራሳቸው የመረጃ ማዕከል እንዲሁም ለማዕከሉ አስፈላጊ የሆኑ መሰረተ ልማቶችን መገንባት ሳያስፈልጋቸው ካሉበት ሆነው የቴክኖሎጂ እና የዲጂታል መፍትሄ አቅራቢዎች ዓለም በደረሰባቸው የቴክኖሎጂ ውጤቶች ተጠቅመው በገነቧቸው እና ደህንነታቸው በተጠበቁ የመረጃ ማዕከላት መረጃዎቻቸውን ማከማችት፣ መቀመር እንዲሁም የተለያዩ አገልግሎቶችን ለማግኘት የሚያስችል ነው” ብለዋል።

ፍሬሕይወት አክለውም የቴሌ ክላውድ ዲጂታል አገልግሎት ድርጅቶች እና ተቋማት ለቴክኖሎጂ መረጣ እና ለስልጠና የሚወስደውን ጊዜ እና የውጪ ምንዛሬ ክፍያ እንደሚያስቀር ገልጸዋል።

የቴሌ ክላውድ ዲጂታል አገልግሎት በሶስት ዓመት የሊድ ስትራተጂ ይሰራሉ ከተባሉ የዲጅታል አገልግሎቶች አንዱ መሆኑን አሳውቀዋል ስራ አስፈጻሚዋ።

[ደመቀ ከበደ ፡ አዲስ አበባ]


1 min read

Published

By Demeke Kebede

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now