SKIP TO MAIN CONTENT

ኢትዮ ቴሌኮም "ቴሌ ክላውድ" ዲጂታል አገልግሎት አስጀመረ

የተለያዩ የዲጂታል አገልግሎቶችን በማስፋፋት ላይ የሚገኘው ኢትዮ ቴሌኮም የቴሌ ክላውድ ዲጂታል አገልግሎት መጀመሩን ዛሬ በሳይንስ ሙዚየም ባካሄደው መርሃ ግብር ይፋ አደርጓል።

Frehiwot Tamiru, CEO of Ethio-Telecom.jpg
Frehiwot Tamiru, CEO of Ethio-Telecom. Credit: EthioTelecom

1 min read

Published

By Demeke Kebede

Source: SBS


Skip to article content

የኢትዮ ቴሌኮም ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ በይፋዊ የማስጀመሪያ ስነ ስርዓቱ ላይእንደገለፁት፤

“የቴሌ ክላውድ አገልግሎት ተቋማት የራሳቸው የመረጃ ማዕከል እንዲሁም ለማዕከሉ አስፈላጊ የሆኑ መሰረተ ልማቶችን መገንባት ሳያስፈልጋቸው ካሉበት ሆነው የቴክኖሎጂ እና የዲጂታል መፍትሄ አቅራቢዎች ዓለም በደረሰባቸው የቴክኖሎጂ ውጤቶች ተጠቅመው በገነቧቸው እና ደህንነታቸው በተጠበቁ የመረጃ ማዕከላት መረጃዎቻቸውን ማከማችት፣ መቀመር እንዲሁም የተለያዩ አገልግሎቶችን ለማግኘት የሚያስችል ነው” ብለዋል።

ፍሬሕይወት አክለውም የቴሌ ክላውድ ዲጂታል አገልግሎት ድርጅቶች እና ተቋማት ለቴክኖሎጂ መረጣ እና ለስልጠና የሚወስደውን ጊዜ እና የውጪ ምንዛሬ ክፍያ እንደሚያስቀር ገልጸዋል።

የቴሌ ክላውድ ዲጂታል አገልግሎት በሶስት ዓመት የሊድ ስትራተጂ ይሰራሉ ከተባሉ የዲጅታል አገልግሎቶች አንዱ መሆኑን አሳውቀዋል ስራ አስፈጻሚዋ።

[ደመቀ ከበደ ፡ አዲስ አበባ]


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Stream now