አዲሱን የ2015 የኢትዮጵያ ዘመን መለወጫ ለመቀበል አምስቱ የጳጉሜን ቀናት የመሪ ሃሳብና የቀናት ስያሜ ተቸራቸው

አምስቱ የጳጉሜን ቀናት የሚከበሩባቸው መሪ ሃሳብና የቀናት ስያሜዎች የተወሰኑት በሚኒስትሮች ምክር ቤት ነው።

Ethiopian fashion models parade during the inauguration ceremony of Sheger park.jpg

Ethiopian fashion models parade during the inauguration ceremony of Sheger park, on September 10, 2020. Credit: AMANUEL SILESHI/AFP via Getty Images

በምክር ቤቱ ውሳኔም መሠረት መሪ ቃሉ "ጳጉሜን በመደመር" የሚል መሆኑን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ደኤታ ከበደ ደሲሳ አስታውቀዋል።

አቶ ከበደ አያይዘውም፤ ለዕለታቱ የተሰጧቸውን ስያሜዎች ገልጠዋል።

በዚህም መሠረት፤

ጳጉሜን 1 - የበጎ ፈቃድ ቀን

ጳጉሜን 2 - የአምራችነት ቀን

ጳጉሜን 3 - የሰላም ቀን

ጳጉሜን 4 - የአገልጋይነት ቀን

ጳጉሜን 5 - የአንድነት ቀን ተብለው ተሰይመዋል።

በእያንዳንዱ የጳጉሜን ቀን ከስያሜው ጋር የተገናኙ መርሃ ግብሮችና ክንዋኔዎች የሚካሔዱ ሲሆን፤ ግብሮቹ የሚከወኑትም በሰላም መደፍረስ ባልታወኩ የኢትዮጵያ ከፍለ አገራት በሙሉ በተመሳሳይ መልኩ ይሆናል።


1 min read

Published

Updated

By Kassahun Seboqa Negewo

Source: SBS



Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now