SKIP TO MAIN CONTENT

አዲሱን የ2015 የኢትዮጵያ ዘመን መለወጫ ለመቀበል አምስቱ የጳጉሜን ቀናት የመሪ ሃሳብና የቀናት ስያሜ ተቸራቸው

አምስቱ የጳጉሜን ቀናት የሚከበሩባቸው መሪ ሃሳብና የቀናት ስያሜዎች የተወሰኑት በሚኒስትሮች ምክር ቤት ነው።

Ethiopian fashion models parade during the inauguration ceremony of Sheger park.jpg
Ethiopian fashion models parade during the inauguration ceremony of Sheger park, on September 10, 2020. Credit: AMANUEL SILESHI/AFP via Getty Images

1 min read

Published

Updated

By Kassahun Seboqa Negewo

Source: SBS


Skip to article content

በምክር ቤቱ ውሳኔም መሠረት መሪ ቃሉ "ጳጉሜን በመደመር" የሚል መሆኑን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ደኤታ ከበደ ደሲሳ አስታውቀዋል።

አቶ ከበደ አያይዘውም፤ ለዕለታቱ የተሰጧቸውን ስያሜዎች ገልጠዋል።

በዚህም መሠረት፤

ጳጉሜን 1 - የበጎ ፈቃድ ቀን

ጳጉሜን 2 - የአምራችነት ቀን

ጳጉሜን 3 - የሰላም ቀን

ጳጉሜን 4 - የአገልጋይነት ቀን

ጳጉሜን 5 - የአንድነት ቀን ተብለው ተሰይመዋል።

በእያንዳንዱ የጳጉሜን ቀን ከስያሜው ጋር የተገናኙ መርሃ ግብሮችና ክንዋኔዎች የሚካሔዱ ሲሆን፤ ግብሮቹ የሚከወኑትም በሰላም መደፍረስ ባልታወኩ የኢትዮጵያ ከፍለ አገራት በሙሉ በተመሳሳይ መልኩ ይሆናል።


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Stream now