የኢትዮጵያ ዘውድ ምክር ቤት የቀድሞው የኢትዮጵያ የመጨረሻው ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የተገደሉበትን 50ኛ ዓመት ዘከረ

"ንጉሠ ነገሥቱ በሁለት ዓለማት መካከል ተይዘው ነበር፤ አንዱ በጣም ጥንታዊ፣ በባሕሉ እና ልማዱ የሚኮራ ፤ ሌላኛው ከሃያኛው ክፍለ ዘመን ጋር እኩል ለመራመድ የተጣደፈ።" የኢትዮጵያ ዘውድ ምክር ቤት

Emperor.png

London, England- Queen Elizabeth II of England rides in an open carriage with Emperor Haile Selassie of Ethiopia. Entering Whitehall from Parliament Square, near Buckingham Palace (L), Emperor Haile Selassie I of Ethiopia (1892 - 1975), 1965 (C), Ethiopian Emperor Haile Selassie in 1936, as he delivered his famed address before the League of Nations. In the speech, he urged the body to save his country from invading Italian forces (R). Credit: Getty Images

የኢትዮጵያ ዘውድ ምክር ቤቱ ንጉሠ ነገሥቱ ሕይወታቸውን ያጡበት ኦገስት 27 / ነሐሴ 21 ቀን በመዘከር ባወጣው መግለጫ፤

"የማይታረቁ የሚመስሉ ፈተናዎችን በመጋፈጥ ንጉሠ ነገሥቱ በእምነት፣ በዲሲፕሊን እና በፅናት በመታገል ለሀገራቸው ዘመናዊነትን ለማምጣት ጥረት በማድረግ አፍሪካን ከቅኝ ግዛት ባርነት ነፃ ለማውጣት ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል" ሲል የአፄ ኃይለ ሥላሴን ሀገራዊና አኅጉራዊ ሚና አመላክቷል።

አያይዞም፤ የጣሊያን ፋሽስት የአምስት ዓመት የወረራ ጊዜ የስደት ሕይወታቸውን በማውሳት፤

"ኢትዮጵያን ነፃ ለማውጣት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ሠርተዋል። ብልህ የፖለቲካና የአመራር ብቃታቸውን ተጠቅመው ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ነፃ አውጥተዋል። የስደት ሸክሙ፣ ኪሳራና ብቸኝነት ቢኖረውም፤ እነዚህን የጭቆና ዓመታት አሸንፈው ስለ መጪው ጊዜያት ለማሰላሰል ተጠቅመውበታል" በማለት አመላክቷል።
gettyimages-74094250-612x612.jpg
Haile Selassie I (previously Prince Ras Tafari), (1891 - 1975), Emperor of Ethiopia, addresses the General Assembly of the United Nations on October 7, 1963, in New York City, New York. Credit: Michael Ochs Archives/Getty Images
ዝክረ መታሰቢያው የንጉሠ ነገሥቱን የሀገር ግንባታ ርዕይና የዘመናዊት ኢትዮጵያ ፈር ቀዳጅነት ጉልህ የአመራር ሚና በመንቀስ፤

"ለትምህርት ትኩረት በመስጠት የኢትዮጵያን ልማት የሚመራና የሚረዳ የተማረ ክፍል ገንብተዋል። በግብርና፣ በትምህርት እና በኢንዱስትሪ ማስፋፋት ትልቅ እመርታን አሳይተዋል። ዘመናዊ የምድር ጦር፣ አየር ኃይል እና ባሕር ኃይልንም መገንባት ችለዋል" ያለ ሲሆን፤ እኒህም የተከወኑት በመከፋፈልና የውስጥ ግጭቶች ውስጥ ተፈትኖ ለስኬት የበቃ እንደነበር አውስቷል።

የዘውድ ምክር ቤቱ መግለጫ ያለፉትን 50 ዓመታት በመዳሰስ፤ ከንጉሠ ነገሥቱ ከዙፋን መነሳትና ሕይወታቸውም በሰው እጅ ማለፍን ተከትሎ ባለፉት አምስት አሠርት ዓመታት ውስጥ ኢትዮጵያን የገጠሟትን ብርቱ ችግሮች ነቅሷል።

"ባለፉት ሃምሳ ዓመታት ውስጥ በሕግ፣ በውክልናና በተጠያቂነት ላይ የተመሰረተ ሥርዓት መፍጠር ተስኖናል። ከታሪካችን ጋር መታረቅ ተስኖናል። ለሕዝባችንና ለሀገራችን የመረጋጋት ርዕይ መቅረፅ ተስኖናል፤ ኢትዮጵያ በሙሉ ልብ ወደፊት አሻግራ እንድታይ የሚያስችል ርዕይ እነሆን ማለት ተስኖናል።

"ኢፍትሐዊነትን ለመዋጋት፣ አፍሪካን ነጻ ለማውጣት እና አፍሪካውያንን በዓለም መድረክ ድምፅ የማሰማት ሥራቸው በታሪክ ውስጥ ተቀርጿል። ለተጨቆኑ ሰዎች ተስፋ ሰጥተዋል። በዓለም ዙሪያ የጥቁር ኩራት ምልክት ሆነዋል። በአፍሪካ አንድነት ድርጅት አማካኝነት የመላው አኅጉር አባት ለመሆን በቅተዋል፤ በራስተፈሪያን አማካኝነት ሉላዊ የጥቁር የነፃነት ንቅናቄ መንፈስን አነሳስተዋል።

AOU.png
Haile Selassie (1892-1975), the Emperor of Ethiopia, opens the conference of the Organisation of African Unity in Addis Ababa, Ethiopia, on 6 February 1973. Credit: William Lovelace/Express/Hulton Archive/Getty Images
የዘውድ ምክር ቤቱ ፕሬዚደንት ልዑል ኤርሚያስ ሳህለ ሥላሴ ኃይለ ሥላሴ ግለ ትውስታቸውን ሲያንፀባርቁ "የልጅ ልጁ እንደመሆኔ፣ በትምህርታችን ላይ እንድንተጋ ያበረታቱን እንደነበር አስታውሳለሁ። ስለ ቤተሰባችን፣ ግዴታችንና ሀገራችን አስተምረውናል።
Prince Ermias.jpg
HIH Prince Ermias Sahle Selassie Haile Selassie, President of the Crown Council of Ethiopia. Credit: Crown Council of Ethiopia
"እግዚአብሔር ሕይወታቸውን እና መታሰቢያቸውን ይባርክ" ብለዋል።

Share

Published

Updated

By Kassahun Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
የኢትዮጵያ ዘውድ ምክር ቤት የቀድሞው የኢትዮጵያ የመጨረሻው ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የተገደሉበትን 50ኛ ዓመት ዘከረ | SBS Amharic