ኢትዮጵያን ጨምሮ ከ46 ሚሊየን በላይ ሰዎች የምግብ እጥረት ገጥሟቸዋል

ግጭት በተካሔደባቸውን የትግራይ፣ አማራና አፋር ክልሎች፤ እንዲሁም በድርቅ ሳቢያ የተጎዱ ክፍለ አገራትን አካትቶ ኢትዮጵያ ውስጥ በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች የምግብ እርዳታ ያሻቸዋል።

gettyimages-935568588-612x612.jpg

A malnourished Somali child sits next to makeshift tents at a camp for people displaced by drought in Mogadishu. Credit: MUSTAFA ABDI/AFP via Getty Images

የአውስትራሊያ የድርጊት ወዳጅነት ይፋ ባደረገው የስድስት ወራት ሪፖርት በምሥራቅ አፍሪካ ከ 46.3 ሚሊየን ሰዎች በላይ ለምግብ እጥረት ተዳረው ያሉ እንዳሉና ድርቅና ግጭት ለክስተቱ አስባብ መሆናቸውን ጠቅሷል።

ምግብና ውኃ ፍለጋ ከቀዬአቸው ርቀው የሚሄዱ ተፈናቃዮች ከሌሎች የአካባቢው ሰዎች ጋር ለግጭት ለመዳረግ እንዳበቃቸውም ገልጧል።

ኢትዮጵያ ውስጥ ለአምስት ተከታታይ የዝናብ ወቅቶች እጥረቶች መከሰት ሁኔታውን ያባብሰው መሆኑንና ቀውሱ ከጎዳቸው ሁለት ሶስተኛዎቹ ሴቶችና ሕፃናት እንደሆኑ አመልክቷል።

የዓለም ምግብ ድርጅት በበኩሉ በትግራይ፣ አማራና አፋር ክልሎች በተከሰቱት ግጭቶች ሳቢያ 9 ነጥብ 4 ሚሊየን ሰዎች የምግብ እርዳታ እንደሚያሻቸው፣ ድርቅ በፈጠረው ረሃብ ሳቢያም በመላ ኢትዮጵያ 11 ነጥብ 8 ሚሊየን ሕዝብ ለረሃብ መጋለጡን አስታውቋል።




Share

Published

By Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
ኢትዮጵያን ጨምሮ ከ46 ሚሊየን በላይ ሰዎች የምግብ እጥረት ገጥሟቸዋል | SBS Amharic