ቪክቶሪያ ከዛሬ የአዲስ ዓመት ዋዜማ ምሽት 5፡00 pm ጀምሮ የሚጸና አዲስ የኮሮናቫይረስ ገደብ ጣለች

*** የቪክቶሪያ ነዋሪዎች ከዛሬ ከምሽቱ 5፡00 pm ጀምሮ ከቤታቸው ውጪ ሲመገቡና ሲጠጡ ካልሆነ በስተቀር በማናቸውም ሁኔታ ቤት ውስጥ ሲታደሙ የፊት ጭምብል ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።

Amharic News 31 December 2020

Melbourne'da sekiz toplum içi vaka tespit edildi. Source: AAP

ቪክቶሪያ ባለፉት 24 ሰዓታት የሶስት ነዋሪዎቿን በኮሮናቫይረስ መያዝ ተከትሎ ከዛሬ ከምሽቱ 5፡00 pm ጀምሮ አዲስ የኮሮናቫይረስ ገደቦችን መጣሏን ተጠባባቂ ፕሪሚየር ጃሲንታ አለን አስታወቁ።

በዚህም መሠረት፦

  • በግለሰብ መኖሪያ ቤት እስከ 30 መሰባሰብ ይፈቀድ የነበረው ወደ 15 ዝቅ ብሏል
  • የፊት ጭምብሎችን በቤቶች ውስጥ ማጥለቅ ግዴታ ሆኗል። ከቤትዎ ለመውጣት ሲያቅዱ የፊት ጭምብል ይዘው ይውጡ፤ ሲመገቡና ሲጠጡ ካልሆነ በስተቀር ከግል መኖሪያዎ ውጪ በማናቸውም የቤት ውስጥ ሁነት ሲታደሙ የፊት ጭምብል ማድረግ ይጠበቅብዎታል። ከገደቡ ጋር ተያይዞ መሥሪያ ቤቶች ሠራተኞቻቸው በቢሮ የሥራ ገበታቸው ላይ ሲገኙ ጭምብሎችን እንዲያጠልቁ መመሪያዎችን ማስተላለፍ ጀምረዋል።
  • አስቀድመው ያስያዙት ጉዳይ ከሌለዎት ወደ ከተማ አይሂዱ
  • በቤት ውስጥ ሁነት የፊት ጭምብል ያጥልቁ
  • መልካም የእጅ ሥነ ንጽሕናን ይተግብሩ
  • ሕመም ከተሰማዎት ቤትዎ ይቆዩ
ለአዲሱ ገደብ መጣል አስባብ የሆኑትና ወሸባ እንዲገቡ ግድ የተሰኙት ሶስት ሴቶች የቫይረስ ጥቃት ከሲድኒ ከተከሰተው ኮሮናቫይረስ ጋር የተገናኘ ነው ብሎ የቪክቶሪያ መንግሥት ያምናል።  

አንደኛዋ የቫይረሱ ተጠቂ ሴት ዕድሜያቸው በ70ዎቹ ውስጥ ያለ ሲሆን፤ ሌሎቹ ሁለቱ ሴቶች በ40ዎቹ ዕድሜ ውስጥ ያሉ ናቸው። መኖሪያችውም በሜልበርን ሚትቻም፣ ሃላምና ሜንቶን ቀበሌዎች ናቸው። 

ቪክቶሪያ ያለ አንዳች የማኅበረሰብ ቫይረስ ተጋቦት 60 ቀናትን በተከታታይ አስቆጥራለች። 

በሌላ በኩል ባለፉት 24 ሰዓታት ኒው ሳዝ ዌይልስ ውስጥ 10 ሰዎች በኮሮናቫይረስ ተጠቅተዋል።

በጥቅሉ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 144 ደርሷል። 

 

 

 

 

 

 

 


Share

Published

Updated

By NACA
Presented by Kassahun Seboqa Negewo

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
ቪክቶሪያ ከዛሬ የአዲስ ዓመት ዋዜማ ምሽት 5፡00 pm ጀምሮ የሚጸና አዲስ የኮሮናቫይረስ ገደብ ጣለች | SBS Amharic