ፐርዝ ከተማ ለአምስት ቀናት የኮሮናቫይረስ ገደቦች ተጣሉባት

*** በቀጣዮቹ አምስት ቀናት ውስጥ የቀብር ሥነ ሥርዓት ከ10 ባልበለጡ ለቀስተኞች የሚካሄድ ሲሆን፤ የሠርግ ሥነሥርዓቶችን ማካሄድ አይቻልም።

Amharic News 31 January 2021

Western Australia Premier Mark McGowan. Source: AAP

በመላው ፐርዝ ከተማ ከዛሬ ጃኑዋሪ 31 ከምሽቱ 6 ሰዓት (6pm) ጀምሮ ለአምስት ቀናት ፀንቶ የሚቆይ የኮረናቫይረስ ገደቦች ተጥለዋል።

ለገደቦቹ መጣል አስባብ የሆነውም አንድ 20ዎቹ ውስጥ ያለ የሆቴል ወሸባ የጥበቃ ሠራተኛ ብርቱ በሆነው የእንግሊዝ ተሠራጭ ኮሮናቫይረስ (UK variant) መያዝ ነው።

በጥበቃ ሥራ የተሰማራው ግለሰብ አንድ በዚሁ ቫይረስ የተያዘ ግለሰብ ባለበት የሆቴል መተላለፊያ ይሠራ ነበር።

ይህንኑ ተከትሎ የመስተንግዶ ግልጋሎት መስጫዎች፣ መጠጥ ቤቶችና ክለቦች፤ የአካል ማጠንከሪያና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች፣ የመጫዎቻ ቦታዎችና የእምነት ቤቶች ዝግ ይሆናሉ። 

በነገው ዕለት ይከፈቱ የነበሩ ትምህርት ቤቶችም ለአምስት ቀናት ዝግ ሆነው ይቆያሉ።

ሆኖም፤ ምግብ ቤቶችና ካፌዎች በቁማቸው ለሚያዙ ደንበኞች ግልጋሎቶቻቸውን ለመስጠት ክፍት ሆነው ይቀጥላሉ።

የቀብር ሥነ ሥርዓት ከ10 ባልበለጡ ለቀስተኞች የሚካሄድ ሲሆን፤ በቀጣዮቹ አምስት ቀናት ውስጥ የሠርግ ሥነ ሥርአቶችን ማካሄድ አይቻልም።

የአረጋውያን መጠወሪያ ቤቶችን ልዩ ሁኔታ ካልገጠመ በስተቀር መጎብኘት አይፈቀደም።

የፐርዝ ነዋሪዎች ከቤት ለመውጣት የሚችሉት አስፈላጊ ነገሮችን ከገበያ ለመሸመት፣ ለሕክምና ወይም ለጤና ክብካቤና የረድኤት ተግባራትን ለማከናወን፣ ከአንድ ተጨማሪ ግለሰብ ጋር ከቤትና ጎረቤት ባልራቀ የአንድ ሰዓት የአካል እንቅስቃሴ ለማድረኛ ከቤት ሆኖ ለመሥራት የማይቻል ከሆነ ወደ ሥራ ለመሰማራት ይሆናል።

የምዕራብ አውስትራሊያ ፕሪሚየር ማርክ ማክጋዋን ነዋሪዎች የሕዝብ ትራንስፖርት ሲጠቀሙ ጭምብል የማድረግ ግዴታ እንዳለባቸው ሁሉ ለማንኛውም ምክንያት ከቤት ሲወጡም ጭምብል ማድረግ እንደሚጥጠበቅባቸው አስታውቀዋል። 

 

 


Share

Published

Updated

By NACA
Presented by Kassahun Seboqa Negewo

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service