Watch FIFA World Cup 2026™

LIVE, FREE and EXCLUSIVE

" የአማራ እና የትግራይን ሕዝብ ወንድማማችነት ለማስቀጠል በቁርጠኝነት እንሠራለን " - ዶ/ር ይልቃል ከፋለ፤ የአማራ ክልል ፕሬዚደንት

እነ ወ/ሮ ኬሪያ ኢብራሒምና ዶ/ር አብርሐም ተከስተ ከእስር ተፈቱ

Dr Yilkal Kefale I.jpg

Dr Yilkal Kefale, President of Amhara Regional State. Credit: AMC

የአማራ ክልል ፕሬዜዳንት ዶ/ር ይልቃል ከፋለ ፤ የሚያጋጥሙንን የፖለቲካ ልዩነቶችን በውይይት በመፍታት የአማራ እና የትግራይን ህዝብ ወንድማማችነት ለማስቀጠል በቁርጠኝነት እንሰራለን አሉ።

ይህን ያሉት ለክልሉ ሚዲያ አሚኮ በሠጡት ቃለ ምልልስ ነው።

ዶ/ር ይልቃል ፥ የተፈጠረውን የሰላም ስምምነት ወደ ህዝብ ለህዝብ ግንኙነት በማሳደግ ተደጋግፈን ከችግራችን የምንወጣበትን መንገድ ማመቻቸት አለብን ብለዋል።

" የፖለቲካ ልዩነትን በውይይት ከመፍታት ይልቅ ጦርነትን አማራጭ ማድረግ መፍትሄ አልባ ኪሳራ እንደሚያደርስ አስተምሮናል " ያሉት ዶ/ር ይልቃል ቀድሞውኑ ችግሮች በሰላማዊ መንገድ ተፈተው ቢሆን ፣ በውይይት እና ድርድር ተፈተው ቢሆን ፣ በሽምግልናና በሰለጠነ አግባብ ተፈተው ቢሆን ይህ ሁሉ ችግር እና ምስቅልቅል በሀገሪቱ ላይደርስ ይችል ነበር ሲሉ ገልጸዋል።

ዶ/ር ይልቃል ፤ ጦርነት ከሰብዓዊ እና ቁሳዊ ጉዳት ባለፈ ስነልቦናዊ ስብራትን እንደሚያስከትል የአማራ እና ትግራይ ህዝብ በተግባር አይተዋል ያሉ ሲሆን " የአማራ ክልል ህዝብ የትግራይ ህዝብ ወንድሙ እንደሆነ ድሮም አብሮ ይኖር ነበር ወደፊትም ቢሆን አብሮ ለመኖር የተዘጋጀ ህዝብ ነው ፤ ከወንድሙ ጋር የሚያጋጥመውን ችግር በሰላም እና በድርድር ለመፍታት ነው የሚዘጋጀው የሚያስበው። የትግራይ ክልል ከኛ የሚጠይቀው ጉዳይ ካለ በሰላም በውይይት ፣ ከዚያም ባለፈ በህግ መፍታት እንችላለን ይሄን የሰለጠነ መንገድ ሁላችንም ተቀብለን መፈፀም አለብን " ብለዋል።

ፕሬዝዳንቱ ጦርነቱ የፈጠረውን ቁስል በሚያክም መንገድ መግባባት ፣ መገናኘት እንደ አንድ ሀገር ዜጋ እንደ ወንድም እና እህት ማህበረስብ መተሳሰብ ይገባናል ብለዋል።

" በዚህም ረገድ የአማራ መንግስትም ሆነ የአማራ ህዝብ የትግራይ ህዝብ የኔ ወንድም እና እህት ነው ብሎ የሚያስብ በችግሩ ጊዜ የሚደርስ በመሆኑ በዚያ መንፈስ ነው የምናየው ፤ ሰላም አብሮነትን የሚያፀና ፣ የሚያጠናክር ይሆናል ብለን እምነት እናደርጋለን " ሲሉ አክለዋል።

ከእሥር ፍቺ

መንግሥት ክስ የመሠረተባቸውን የሕወሃት ሲቪልና ወታደራዊ አመራሮች ከእስር መፍታቱን የተከሳሾቹ ጠበቃና ቤተሰቦች ገልፀዋል።

ትናንት ከእስር ከተፈቱት መካከል፣ የቀድሞው የትግራይ ክልል ም/ርዕሰ መስተዳድር አብርሃም ተከስተ፣ አዲስዓለም ባሌማ እና የቀድሞዋ የፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ኬሪያ ኢብራሂም ይገኙበታል።

ከእስር የተፈቱት ተከሳሾች፣ በደብረጺዮን ገ/ሚካዔልና በጀኔራል ታደሠ ወረደ መዝገብ ስር ክስ ተመስርቶባቸው የነበሩ 16 ሲቪልና 20 ወታደራዊ መኮንኖች ናቸው።

ተከሳሾቹ የተፈቱት፣ ፍትህ ሚንስቴር በፓርቲው ሲቪልና ወታደራዊ አመራሮች ላይ የከፈተውን ክስ ማቋረጡን ተከትሎ ነው።


2 min read

Published

By Stringer Report

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now