" የአማራ እና የትግራይን ሕዝብ ወንድማማችነት ለማስቀጠል በቁርጠኝነት እንሠራለን " - ዶ/ር ይልቃል ከፋለ፤ የአማራ ክልል ፕሬዚደንት

እነ ወ/ሮ ኬሪያ ኢብራሒምና ዶ/ር አብርሐም ተከስተ ከእስር ተፈቱ

Dr Yilkal Kefale I.jpg

Dr Yilkal Kefale, President of Amhara Regional State. Credit: AMC

የአማራ ክልል ፕሬዜዳንት ዶ/ር ይልቃል ከፋለ ፤ የሚያጋጥሙንን የፖለቲካ ልዩነቶችን በውይይት በመፍታት የአማራ እና የትግራይን ህዝብ ወንድማማችነት ለማስቀጠል በቁርጠኝነት እንሰራለን አሉ።

ይህን ያሉት ለክልሉ ሚዲያ አሚኮ በሠጡት ቃለ ምልልስ ነው።

ዶ/ር ይልቃል ፥ የተፈጠረውን የሰላም ስምምነት ወደ ህዝብ ለህዝብ ግንኙነት በማሳደግ ተደጋግፈን ከችግራችን የምንወጣበትን መንገድ ማመቻቸት አለብን ብለዋል።

" የፖለቲካ ልዩነትን በውይይት ከመፍታት ይልቅ ጦርነትን አማራጭ ማድረግ መፍትሄ አልባ ኪሳራ እንደሚያደርስ አስተምሮናል " ያሉት ዶ/ር ይልቃል ቀድሞውኑ ችግሮች በሰላማዊ መንገድ ተፈተው ቢሆን ፣ በውይይት እና ድርድር ተፈተው ቢሆን ፣ በሽምግልናና በሰለጠነ አግባብ ተፈተው ቢሆን ይህ ሁሉ ችግር እና ምስቅልቅል በሀገሪቱ ላይደርስ ይችል ነበር ሲሉ ገልጸዋል።

ዶ/ር ይልቃል ፤ ጦርነት ከሰብዓዊ እና ቁሳዊ ጉዳት ባለፈ ስነልቦናዊ ስብራትን እንደሚያስከትል የአማራ እና ትግራይ ህዝብ በተግባር አይተዋል ያሉ ሲሆን " የአማራ ክልል ህዝብ የትግራይ ህዝብ ወንድሙ እንደሆነ ድሮም አብሮ ይኖር ነበር ወደፊትም ቢሆን አብሮ ለመኖር የተዘጋጀ ህዝብ ነው ፤ ከወንድሙ ጋር የሚያጋጥመውን ችግር በሰላም እና በድርድር ለመፍታት ነው የሚዘጋጀው የሚያስበው። የትግራይ ክልል ከኛ የሚጠይቀው ጉዳይ ካለ በሰላም በውይይት ፣ ከዚያም ባለፈ በህግ መፍታት እንችላለን ይሄን የሰለጠነ መንገድ ሁላችንም ተቀብለን መፈፀም አለብን " ብለዋል።

ፕሬዝዳንቱ ጦርነቱ የፈጠረውን ቁስል በሚያክም መንገድ መግባባት ፣ መገናኘት እንደ አንድ ሀገር ዜጋ እንደ ወንድም እና እህት ማህበረስብ መተሳሰብ ይገባናል ብለዋል።

" በዚህም ረገድ የአማራ መንግስትም ሆነ የአማራ ህዝብ የትግራይ ህዝብ የኔ ወንድም እና እህት ነው ብሎ የሚያስብ በችግሩ ጊዜ የሚደርስ በመሆኑ በዚያ መንፈስ ነው የምናየው ፤ ሰላም አብሮነትን የሚያፀና ፣ የሚያጠናክር ይሆናል ብለን እምነት እናደርጋለን " ሲሉ አክለዋል።

ከእሥር ፍቺ

መንግሥት ክስ የመሠረተባቸውን የሕወሃት ሲቪልና ወታደራዊ አመራሮች ከእስር መፍታቱን የተከሳሾቹ ጠበቃና ቤተሰቦች ገልፀዋል።

ትናንት ከእስር ከተፈቱት መካከል፣ የቀድሞው የትግራይ ክልል ም/ርዕሰ መስተዳድር አብርሃም ተከስተ፣ አዲስዓለም ባሌማ እና የቀድሞዋ የፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ኬሪያ ኢብራሂም ይገኙበታል።

ከእስር የተፈቱት ተከሳሾች፣ በደብረጺዮን ገ/ሚካዔልና በጀኔራል ታደሠ ወረደ መዝገብ ስር ክስ ተመስርቶባቸው የነበሩ 16 ሲቪልና 20 ወታደራዊ መኮንኖች ናቸው።

ተከሳሾቹ የተፈቱት፣ ፍትህ ሚንስቴር በፓርቲው ሲቪልና ወታደራዊ አመራሮች ላይ የከፈተውን ክስ ማቋረጡን ተከትሎ ነው።

Share

Published

By Stringer Report
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service