22ኛው "ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ" በድምቀት ተካሄደ

ዛሬ የተካሔደው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ መነሻው እና መጨረሻው መስቀል አደባባይ ያደረገ ሲሆን አጠቃላይ ርቀቱም 10 ኪሎ ሜትር ነው፡፡

A crowd awaits to participate in the 21st edition of the Great Ethiopian Run, in the city of Addis Ababa, Ethiopia, on November 20, 2022.jpg

A crowd awaits to participate in the annual 10k run of the Great Ethiopian Run, in the city of Addis Ababa, Ethiopia, on November 20, 2022. Credit: PR

ታዋቂ አትሌቶችን ጨምሮ ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች የተሳተፉበት ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በአዲስ አበባ ከተማ በድምቀት ተካሂዷል፡፡

ፕሬዝደንት ሳሕለወርቅ ዘውዴ፣ ከንቲባ አዳነች አቤቤና ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ ሩጫውን አስጀምረውታል።
Ethiopian President and Mayor of Addis Ababa.jpg
Ethiopian President Sahlework Zewde (L), and Adanech Abiebie, Mayor of Addis Ababa (C). Credit: PR
ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በ1994 ዓ.ም በአትሌት ኃይሌ ገብረ ሥላሴ የተጀመረ ሲሆን በአፍሪካ ቀዳሚ በዓለም ደግሞ ስድስተኛ ደረጃ ላይ የሚገኝ ትልቅ የጎዳና ላይ ሩጫ ነው፡፡

ዛሬ የተካሔደው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ መነሻው እና መጨረሻው መስቀል አደባባይ ያደረገ ሲሆን አጠቃላይ ርቀቱም 10 ኪሎ ሜትር ነው፡፡

ከዚህኛው ሩጫ ቀደም ብሎ ትናንት የህፃናት ዛሬ ደግሞ የአካል ጉዳተኞች ውድድር ተካሂዷል፡፡
Wheelchair Runners.jpg
Wheelchair racers. Credit: PR
የ 2015 ሶፊ ማልት ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በዛሬው ዕለት 40,000 ራጮች ታድመውበታል።

በውድድሩ አትሌቶች በ 10 ኪ.ሜ ሩጫ በወንዶች እና በሴቶች ዘርፍ የተወዳደሩ ሲሆን በወንዶች አቤ ጋሻሁን በአንደኝነት፣ ሀይለማርያም አማረ በሁለተኝነትና ገመቹ ዲዳ ደግሞ በሶስተኝነት ውድድሩን አጠናቀዋል። አቤ ጋሻሁን በታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ውድድር ሲያሸንፍ የዘንድሮው ለሶስተኛ ጊዜ ነው።

በሌላ መልኩ ደግሞ ትዕግስት ከተማ ቀዳሚ ሆና ስታጠናቅቅ ፡ መስታወት ፍቅር ሁለተኛ እንዲሁም ፎቴን ተስፋዬ ሶስተኛ በመውጣት የዘንድሮው የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የሴቶች ዘርፍ አሸናፊዎች መሆናቸው ታውቋል።

[ ደመቀ ከበደ ፡ አዲስ አበባ ]

Share

Published

By Demeke Kebede
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
22ኛው "ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ" በድምቀት ተካሄደ | SBS Amharic